Thursday 1 August 2013

የህጻናት ጥምቀት

በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት እና በፕሮቴስታንቶች በጥምቀት ላይ ያለ ልዩነት

በጥምቀት ላይ ያለው ልዩነት በአምስት ከፍለን ሊጠቃለል ይችላል እነዚህም ፡-

1. በኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት በጥምቀት ድህነትን፣ መንጻትን፣ ፍትህን፣ አዲስ ሕይወትንና በክርስቶስ ክርስቲያን መሆንን ያስገኛልን ወይስ እንደ ፕሮቴስታንት እምነት እነዚህ ሁሉ በማመን ብቻ ይገኛል; በማመን ብቻስ ከሆነ ለምን መጠመቅ ያስፈልጋል ታድያ

2. መጠመቅ የክርስቲየን ምልክት ነው ወይስ ጌታ ስላዘዘ ብቻ ለትዕዛዙ ሲባል ነው፡፡ የምንጠመቀው /ማቴ.28፣19/

3. እኛ ጥምቀትን ከሚሰጥራተ ቤተክርስቲያን አንዱ ነው ብለን እናምናለን ፕሮቴስታንቶች ግን ይህንን አያምኑም፡፡

4. እኛ ውሀ ውስጥ እናጠምቃን እነርሱ ግን በመርጨት ያጠምቁም፡፡

5. እኛ ህፃናን ስለቤተሰቦቻቸው እምነት እናጠምቃለን፣ ፕሮቴስታንቶች ግን ሕፃናትን በማጥመቅ አያምኑም ምከንያቱም ሲሰጡ ‹‹ከጥምቀት ማመን መቅደም አለበት›› ይላሉ፡፡

የፕሮቴስታቶች የተቃውሞ ነጥቦች

1. ጥምቀት ባይኖር እምነት ብቻውን አይበቃምን?

2. የተሰቀለው ወንበዴ/ፈያታዊ ዘየማን/ሳይጠመቅ እንዴት ዳነ?

3. ውሃ ልጅነት አዲ ሕይወትን ሊሰጥ ይችላልን?

4. ጥምቀት የሕይወት መታደስ ከሆነ ለምን ደግመን እንበድላለን? /ኃጢያት እንሰራለን/

5. አንድ ሕፃን ከተጠመቁና ኃጢያታቸው ይቅር ከተባለላቸው ቤተሰቦች ከተወለደ የቤተሰቦቹን ኃጢያት እንዴት ሊወርስ ይችላል

6. ሐዋያት ስለክርስቶስ እና ስለ ቤተክርስቲያን ግንኙነት ሲገልጽ ባሎች ሆይ ክርስቶስ ደግሞ ቤተክርስቲያን እደወደዳት ሚሰቶቻችሁን ውደዱ በውሃ መታጠብ ከቃሉ ጋር አንፅቶ እንዲቀድሳት ስለ እርስዋ ራሱን አሳልፎ ሰጠ፡፡ /ኤፌ ተ፣26/ ይላል፡፡ ታዲያ በጥምቀት ያው ውሃ የቃል ተምሳት ነውን?

ሕፃናትን ማጥመቅ

የጌታችንን ‹‹ ያመነ የተጠመቀ ይድናል›› የሚለውን ቃል በመንተራስ ፕሮቴስታንቶች ከማጥመቅ ይልቅ እምነት ይቀድማል በማለት ሕፃናጽን አያጠምቁም፡፡ ታዲያ ጥምቀት ያለ እምነት እምነትና እውቀት እንዴት ይከናወናል

እኛ ግን ሕፃናት እንዲጠመቁ እንላለን፡፡ ምክንያም፡-

ሀ. እኛ የምናስበው ስለ ሕፃና ሰማያዊ ሕይወት ነው፡፡ የኸውም ጌታችን ‹‹እውነት እልሃለሁ ሰው ከውሃና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግሥት ሊገባ አይችልም፡፡›› /ዩሐ.3.5/ ስላለ ነው፡፡ ታዲያ ስለምን ሕፃናትን አናጠምቅም? ስለምንስ ለእግዚአብሄር ፍርድ አሳልፈን እንሰጣቸዋለን? ጌታችን የላይኛውን ኃይለ ቃል ሲናር ሕፃናትን አልተወም፡፡

ለ. በማጥመቅ ሕፃናት የቤተ ክርስቲያን ሕይወት ይለማመዱታል፡፡ በጥምቀት መንፈሳዊ ጥቅም እና፣ የሰማያዊውን ምስጢር ደስታ ያገኛሉ፣ በቤተክርስቲያን ውስጥ ያሉ ፀጋን የሚያሰጡ ምስጢራትን ውጤታቸውን በሕይወታቸው ይቀምሱታል፡፡ እኛም በዚህ መንገድ ሕፃናን ለክርስትና ሕይወት በተግባር እንዲዘጋጁ እናደርጋቸዋለን፡፡ ከቤተ ክርስቲያ ካገለልናቸው ግን እምነትንና የፀጋ ምክንያቶችንም መከልከላችን ነው፡፡

ሐ. ‹‹ ያመነና የተጠመቀ ይድናል›› የሚለው የጌታ አባባል የጎልማሶችን እምት የሚያመለክት ነው፣ ምንያቱም ጎልማሶች ሊያመዛዝኑ ስለሚችሉ ነው፡፡ ስለዚህም ነው እኛ ጎልማሶችን ካላመኑ የማናጠምቃቸው፣ ለሕፃናት ግን ‹‹ሕፃናትን ተውአቸው ወደ እኔም ይመጡ ዘንድ አትከልክሏቸው፡፡ መንግሥተ ሰማያት እንደነዚህ ላሉ ናትና፡፡›› /ማ.19.14/ የሚለው የቤታችን ቃል ተፈጻሚ ይሆናል፡፡

ከእምነት አንፃር ሕፃናት ሁሉንም ነገር ሊቀበሉና ሊያምኑ በሚችሉበት ሁኔታ ላይ ነው ያሉት፣ እምነትን አይቃረኑም ወይም አንቀበልም አይሉም፡፡ በጎልማሶች ነው እንጂ በዓመ ሕፃና መጠየቅና መጠራጠር የለም፡፡ ይህም ከሰማያዊ መንግሥት አያግዳቸውም እነርሱን ማጥመቅ ‹‹ነፃ ድህነት ‹‹ ብለው ከሚያስተጋቡት ከወንድሞችን ከፕሮቴስታንቶች መፈክር ጋር የሚስማማ ነው፡፡

መ. በእምነት ጉደይ ላይ በአነጋገር ጥብቅ ከሆንን፣ የእምነትን ጥልቀትና ምንነት ሊረዱ የማይችሉ እጅግ ብዙ ሰዎችን ለምሳሌ በአእምሮ ያልበሰሉ ጎልማሶችን ያልተማሩ ገበሬዎችን ወዛደሮችን እና ወዘተ . . . ነገረ መለኮታዊ እውነታዎችን ሊያውቁ የማይችሉ ሰዎ የቱ ድረስ ነው የእምነታቸው ሁኔታ ታድያ እንደ ሕፃናት መጠመቅን ልንከለክላቸው ይገባልን? ብለን እንጠይቃን፡፡

ሠ. አንዳዶች ሕፃናት ሲያድጉ እምነቱን ቢተውትስ? ብለው ይጠይቃሉ፡፡ ያ ሕፃን እንደ ከሃዲ ይቆጠራል ምክያቱም በጥምቀት የተቀበለውን ፀጋ በነፃ ፈቃዱ ክዷል፡፡ እኛ ግን ስለሱ ያብንን ግዴታችንን ተወጥተናል፡፡ ሌላው ጉዳይ ሁሉ ለእርሱ የሚተው ነው፡፡ ‹‹እርሱም በመንፈስ እንደ ጀመረ አሁን ደግሞ በስጋ ሁሉን ለመፈጸም እንደሚሞክር ሆኖአል፡፡ እንግዲህ የማታስተውሉ ናችሁ? በመንፈስስ ጀምራችሁ አሁን በሥጋ ትፈጽማላችሁን? /ገላ.33/እንዳ ሐዋርያው ምናልባትም የተጠመቁና ሕይወታቸው በቤተክርስቲያን የሆነ ትንሽ ሕፃናት የእግዚአብሔር ፀጋ ስለ ቀመሱ፣ እስኪያድጉ ድረስ ትንንሽ ሕፃናት የእግዚብሄር ፀጋ ስለ ቀመሱ፣ እስኪያድጉ ድረስ ካልተጠመቁት ይልቅ ለክህደት ብዙ የተጋጡት አይሆኑም፡፡

ረ. ሕፃናትን ማጥመቅን የማያምኑ፣ በርግጥ በጥምቀት መዳን እንደሚገኝ የሚክዱ ናቸው/ ማር.16.16/ ምክንያቱም ጥምቀት ለመዳ እንደሚያስፈልግ ቢያምኑ ኖሮ ሕፃናትን ከድኅነት ባለከለከሏቸውም ነበር፡፡ ደግሞ እምነት የሌላቸው ስለሆነ ያላመኑትና ያልተጠመቁት ሕፃናት መድረቸው የት ነው? ጥያቄው መልስ የለውም

ሸ. መጽሐፍ ቅዱሰ ይህን ስለሚያመለክት እኛ ሕፃና እናጠምቃለን፡፡ መጽሐፍ ቅዱስ የሙሉ ቤተሰብን መጠመቅ ወይም አንድ ሰው ራሱና ቤተሰቡ ሁሉ ሲጠመቁ ያለክታ፡፡ ታዲያ በነዚህ ቤተሰቦች ውስጥ ሕፃናት እደነበሩ ምም ጥርጥር የለውም፡፡

እነዚህ ጥቂት ምሳሌዎች ናቸው፡፡

- በፊሊጲያ ለወኀኒ ጠባቂው ቅዱስ ጳውሎስና ሊላስ ‹‹ በጌታ ኢየሱ ክርስቶስ እመን አንተና ቤተሰቦችህም ትድናላችሁ/ ሐወ.16፣315/ አሉት፡፡ ይህ ማት የጠባቂው እምት የመጀመሪያ እምነት ሆኖ ቤተሰቡን ወደ ድኃነት ይመራ፡፡ ከዚያ በኃላ ነው ‹‹ለእርሱና በቤቱም ላ ሁሉ የእግዚአብሄርን ቃል ተናገሩላቸው፡፡ በሌሊትም በዚያች ሰዓት ወስዶ ቁስላቸውን አጠበላቸው ያን ጊዜውንም እርሱ ከቤተሰቦቹ ጋር ተጠመቀ፡፡›› /የሐዋ.ሥራ 16፣32/ የተባለው፡፡ መጽሐፍ ቅዱ ከወኀኒ ጠባቂው ቤተሰብ ሕፃናትን ያለጥርጥር ቸምሮ ነው፡፡

• የቀይ ሃር ሻጭዋ የሊዲያ ጥምቀት ‹‹ እርሷ ከቤተሰቦቿ ጋር ከተጠመቀች በኃላ ‹‹/የሐ.ሥራ 16፣15/ተብሎ ተጽፏል፡፡

• ቅዱስ ጳውሎስ ‹‹የእስጢፋስንም ቤተሰቦዎች ደግሞ አጥምቄአለሁ ጨምሬ ሌላ አጥምቄ እንደሆነ አላውቅም›› /1ኛ ቆሮ.1፣16/አለ ታዲያ እነዚህ ሁሉ ቤተሰቦች ያለ ሕፃን ይሆናሉ?

• በእለተ ጴንጤቆስጤ ከተጠመቁት መካከል ህናፃና ያለመኖራቸውን መጽሐፍ ቅዱስ አያመለክትም፡፡

በታሪክም ህፃናትን ማጥመቅ ተጽፎ ይገኛል፡፡ ስዚህም በቅዱስ ወይንስ የተወለደ?/ የተደረገውን ክርክር እንጠቅሳለን፡፡ ቅዱስ አውግስቲን ከሰው የሚወለድ ነው ›› አለ፡፡ ቅዱስ ጀሮም ደግሞ ‹‹የሚፈጠር›› ነው አለ፡፡ ቅዱስ አውግስቲንም የሚፈጠር ከሆነ የአዳምን ኃጢያት አይወርስም፡፡ ስለዚህ ለምን ህፃናትን እናጠምቃን? ሲል ጠይቆታል፡፡ ቅዱስ ጀሮም ለዚህ ሊመልስ አልቻለም፡፡

ሕፃናትን ማጥመቅ የሚከለክል አንድ ጥቅስ እንኳን በመጽሐፍ ቅዱስ የለም፡፡

ከእምነት አንፃር፣ ሕፃናትን ስለቤተሰቦቻቸው እምነት እናጠምቃለን፡፡ ይህም በመጽሐፍ ቅዱስ ብዙ ምሳሌዎች አሉት ለምሳሌ፡-

ሀ. የኦሪቱ ግዝረት የጥምቀት ምሳለ ነው ቀድሞ እንደገለጽነው የተገረዘው ከእግዚአብሔር ሕዝብ ይቆጠር ነበር ምክንያቱም በእግዚአብሔርና በአብርሃምና መካከል በተደረገው ኪዳ መሰረት ‹‹የሸለፈታችሁንም ሥጋ ትገርዛላችሁ በእኔና በእናነተ መካከል ላለው ቃል ኪዳኔ ምልከት የሆናል፡፡ ተብሎአል፡፡ /ዘፍ.7፣11/ ይህም ግዝረት የሚደረገው ሀፃኑ ከተወለደ በ89 ቀን መሆኑ የታወቀ ነው፡፡ ታዲያ በአብርሃምና በእግዚአብሔር መካከል ስላለው ኪዳ የ80 ቀን ህፃን ም ያውቃልን? ከእግዚአብሔር ህዝብ ጋር አንድነት መደመሩንስ ያውቃልን? ስለተስፋውስ ምን ያውቃል? ያጥርጥ እንዲህ ያለ ነገር አያውቅም፡፡ ነገር ግን ስለቤተሰቦቹ እምነት ተገርዞ የእግዚአብሔር ሕዝብ አባልና እግዚብሔር ለአባታችን ለአብርሃም የሰጠው የተስፋው ቃል ተካፋይ ይሆናል፡፡

ለ. ቀይ ባህርን መሻገር የጥምቀት ምሳሌ ነበር፣ ወይም ደግሞ በራሱ ጥምቀት ነበር ቅዱስ ጳውሎስ በመልዕክቱ ‹‹ሁሉም ሙሴን ይተባበሩ \ዘንድ በደመናና በባህር ተጠመቁ ሁሉም ያን መንፈሳዊ መብል በሉ፡፡›› 1ኛ ቁሮ.10፣2/በማለት እንዳስረዳው፡፡ ይኸውም ከሞ ከሰይጣንና ከኃጢያት ባርነት የመውጣት ምሳሌ ነው፡፡ ቀይ ባህርን የተሸገሩ ጎልማሶች ናቸው፡፡ እነርሱም እግዚአብሄር ለሙሴ የሰጠውን ተስፋ ጠንቅቀው ያውቁ ነበር፡፡ ለፈርኦን ባሮች እንደነበሩም፣ ከባነት በኃላ በእግዚአብሄር ኃይል መዳናቸውንም ጭምር ያውቃሉ ሕፃናቱም ቀይ ባህርን በተሻገሩ ጊጊ/ሲጠመቁ/ ድነዋል፣ ከባርነት ነፃ መጥተዋል፣ ተጠምቀዋል፡፡ ታዲያ ይ የተደረገላቸው በራሳቸው እምነት አልነበረም ነገር ግን በቤተሰቦቻቸው እምነት ነው እንጂ፣ ምንያቱም እነዚህ ህፃናት የተፈጸሙትን ሁኔታዎች አያውቋቸውም እነዚህ ህጻናት የተፈጸሙትን ሁኔታዎች አያወቀቋቸውም፡፡

ሐ. ሌላው እጅግ ጠቃሚ ምሳሌ በፋሲካው ጠቦት ደም የህፃናተ መዳን ነበር፡፡ ይኸውም በኩርን ከሚገድለው መልአክ እጅግ ይድኑ ዘንድ እግዚአብሄር ሙሴን የአንድ አመት ነውር የሌለበት ወንድ ፍየል ወይም በግ እንዲያርድና ደሙንም በበሮቻቸው መቃንና ጉበን እንዲቀቡት አዘዛቸው፡፡ ‹‹ደሙንም ባየሁ ጊዜ ከእናንተ አልፋለሁ፡፡››/ዘጸ.12፣13/ አላቸው፡፡

- ሐዋርያው የጠቦቱ ደም ድኀነት ያገኘንበት የኢየሱ ክርስቶ ደም ምሳሌ መሆኑ ‹‹ፋሲካችን ክርስቶስ ታርዷልና››/1ቆሮ.5፣5/ በማት አስረዳን፡፡

- ፋሲካው በግ ደም የዳኑት የነዚህ ህፃናት እምነት ምን ነበር? በጌታና በሙሴ መካከል ስለነበረው ኪዳን ወይም ስለፋሲካና በፋሲካው በግ ደም ከሞት ስለመዳን ምንያውቃሉያለጥርጥ ምንም አያውቁም፡፡ ነገር ግን ስለደሙ ጥቅም የፋሲካው በግ ደም ከሞት እንደሚያድን ቤተሶበቻቸው ስላመኑ ህፃነቱ ከሞት ድነዋል፡፡ በመገረዝ በፋሲካው ደምና ታላቁን ባህር በመሻገር የዳኑ ህጻናት እንዚህ ሁሉ ም መሆናቸውን ካደጉ በኃላ አውቀዋቸዋል በመሆኑም ድኅነትን ያለዋጋ ቀድመው አግኝተዋል፡፡

- ቤተሰቦቻቸው በእግዚአብሔር እና በሰዎች መካል በተደረጉ ተስፋዎችና ቃልኪዳኖች ስላመኑ ልጆቹም ሲያድጉ ወደ እምነቱ በተግባር ገብተዋል፡፡

(አንጻራዊ ትምህርተ መለኮት)

No comments: