Thursday 19 January 2012

“ተጠምቀ ሰማያዊ በእደ መሬታዊ”

“Epiphany
God Holy might, Holy living, immortal who was baptized in the Jordan & crucified on the cross have mercy up on us.

ባሕር አየች ሸሸችም፤
ዮርዳኖስም ወደ ኋላው ተመለሰ፤
ተራሮች እንደ አውራ በግ፤ ኮረብቶችም እንደ ጠቦት ዘለሉ፤
በእንስሳት በረት ተጨመረ ፤
የንጉሥንም እጅ መንሻ ተቀበለ ፤
ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕፃናት አለቀሰ።
በግልጥ ተመላለሰ፤ እንደ ሰውም ታየ፤
በየጥቂቱ አደገ በሠላሳ ዘመን በዮርዳኖስ ተጠመቀ”
 ቅዳሴ ዲዮስቆሮስ ወመዝሙረ ዳዊት [መዝ 113: 3]

v  በሃገራችን ጥምቀት በግሩም ሁኔታ ይከበራል፤
ታቦታቱ ከመንበራቸው ወተው ውሃ ወዳለበት ሄደው ያድሩና ወደ መንበራቸው ይመለሳሉ። ይህ ለምን ይሆን? ቢሉ ምሳሌው ግሩም ነው፤ ይህም ጌታ ከገሊላ ወደ ዮርዳኖስ ሄዶ የመጠመቁ ምሳሌ ነው ይህ በየትኛውም አለም የሌለ በሃገራችን ብቻ ያለ ድንቅ ሥርአት ነው።
v  ማየ ገቦ፦ ሀብተ ንጽህ ሀብተ ክቡር የሚሆን ቅዱስ
ሥጋውን ከኃጢአት የምንድንበትን ማየ ገቦን /ከጎኑ የፈሰሰውን ውሃ/ ሰጠን።
vጌታችን በእደ ዩሐንስ በባህረ ዩርዳኖስ ከለሊቱ በ10 ሰዓት
ተጠመቀ። ለምን ተጠመቀ ቢሉ ዲያቢሎስ አዳም ገብሩ ለዳያቢሎስ ሔዋን አመቱ ለዲያቢሎስ ብሎ በሁለት ጽላት የእዳ ደብዳቤ ጽፎ አንዱን በዮርዳኖስ አንዱን በሲኦል አስቀምጦት ነበረና ጌታችን በዮርዳኖስ ተጠምቆ ያንን የእዳ ደብዳቤውን ደመሰሰው። በሲኦል የነበረውን ደግሞ በእለተ አርብ ደምስሶታል፤ [በእኛ ላይ የነበረውን የእዳ ጽህፈት ደመሰሰው እንደሚል ቆላስይስ 2:11]

v                   ለመጀመሪያ ግዜ በዓለም ላይ ጥምቀትን የተጠመቀ ኢትጲያዊው ጃንደረባ [ባኮስ] ሲሆን ለመጀመሪያ ግዜ በዓለም ላይ ያጠመቀ ደግሞ ሐዋርያው ፊሊጶስ ይሆናል ማለት ነው።
      የአመነ የተጠመቀ ይድናል ማር16:16    ባኮስ ሲጠመቅ                                        
v  ጌታችን ስለምን ተጠመቀ ቢሉ አንድም ለቀድሶተ ማይ
/ውሃን ለመቀደስና/ ለቀድሶተ ጥምቀት ጥምቀትን ቀድሶ ለመስጠት ነው። አንድም ለምሳሌነት ነው፤ አንድም ዮርዳኖስ ወደ ሗላዋ ሸሸች የተባለው ትንቢት ለመፈጸም ነው። አንድም ለምን በ30 ዓመቱ ተጠመቀ ቢሉ አዳም የ30 አመት ጉልማሳ ሆኖ ተፈጠረና ገነት ርስቱን አጣት; በ30 አመቱ ያጣትን ገነትን ለመመለስ ጌታችን በ30 ዓመቱ ተጠመቀ። አንድም ስለምን ወንድ በ40 ቀን ሴት በ80 ቀን ይጠመቃሉ ቢሉ አዳም በተፈጠረ በ40 ቀኑ ሔዋን በተፈጠረች በ80 ቀኗ ገነትን አግኝተዋልና እኛም መንግስተ ሰማያትን ለመውረስ በ40ና 80 ቀናችን እንጠመቃለን። 
vAnna Baptist [ዳግም አጥማቂዎች]
እነዚህ የፕሮቴስታንት ክፍሎች ሲሆኑ በሥላሴ አንድነትና ሶስትነት ስለማያምኑ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ከተጠመቅን በሗላ ዳግም በኢየሱስ ክርስቶስ ስም መጠመቅ አለብን የሚሉ ናቸው፤ ጥምቀት ግን አትደገምም አትከለስምም
አንድ ጌታ አንዲት ጥምቀት” እንዲል ኤፌሶን [4:4]
 


ጾመ ገሃድ፦ በጥምቀት ቀን ጾም ፈጽሞ አይጾምም፤ ጥምቀት እሮብና አርብ ቢውል እንኳን አይጾምም፤

ጥምቀት እሮብ ቢውል ማክሰኞ፤ አርብ ቢውል ሐሙስ ይጾማል።

ሐሙስ ቢውል ማክሰኞ፤ ቅዳሜ ቢውል ሐሙስ ይጾማል። ይህም የገሃድ ጾም ይባላል።

ጥያቄና መልስ፦

ለመዳን የግድ መጠመቅ ያስፈልጋል፤ ያመነ የተጠመቀ ይድናል ስለሚል ማር16:16፤ ይህ ከሆነ ፈያታዊ ዘየማን ተጠምቆ ነው ወይስ እንዴት ነው ገነት የገባው?


መልስ

የድሮ ክርስቲያኖች ለጥምቀት በሚሄዱበት ግዜ ገና በመንገድ ላይ እያሉ ሰማዕትነት ይቀበሉና በደማቸው ይጠመቁ ነበር፤ እነዚህ ደመ ሰማዕታት ሲባሉ ዋጋውም ከፍተኛ ነው 1ኛ ዩሐ. 5:6


ፈያታዊው ዘየማን የጌታ ደም ደመ ጥምቀት” ሆኖለት
ወደ ገነት ለመግባት
የመጀመሪያው ሰው ሆኗል!!

                        
[ተክለ መድህን]


Monday 16 January 2012

“Epiphany”



v     ደውል ተደወለ!

         ካህናቱ ተሰበሰቡ!

         መሪ ጌቶችም ለማህሌት ተነሱ!

         የሰ/ት/ቤት መዘምራን ለመዝሙር ከበሮውን አነሱ!

         ሕዝበ እግዚአብሔርም ተጠራ!

         እነሆ ጥምቀትበከተማችን በለንደን ለመጀመሪያ ግዜ  እጅግ ለየት ባለ ሁኔታ ሊከበር ነው!

         ቅ/ሥላሴ ፣ ጽ/ጽዮን ፣ ቅ/ገብርኤል ቤተክ በአንድነት በመሆን በአውሮፓ የመጀመሪያ የሆነውን ታላቅ     
         በዓል ያከብራሉ፤


v     ቀንና አድራሻ፦

ከአርብ 20 Jan 7pm – ቅዳሜ 21 Jan 12 pm

St Pancras church;


Euston RD
London
NW1 2BA

Nearest station Euston /northern & Victoria line/


v     ይህ ሥርአት ግሩም ነው! እስራኤል አታውቀው አሜሪካም የላት እንግሊዝም አላወቀችው፤ እነሆ አያምልጦት! ከወገናችሁ ጋር በዓሉን ያሳልፉ፤ ኑ በአንድነትም እናክብር !!! ልጆቻችሁን አምጡና የሃገራቸውን ሐይማኖትና ባህላቸውን አሳውቁ! ካሜራችሁም በዛች ቀን ውብ የሆኑ ፎቶዎችንና ቪዲዮችን ለማንሳት እነሆ ብዙ ስራ ይጠበቅበታል!

v     በዚህ በዓል ላይ BBC እና የተለያዩ የእንግሊዝ ባለስልጣኖች ፣ የሃገሪቱ ነዋሪዎች ይገኛሉና ሃገራችንን በመልካም ጎኑ እናስተዋውቅ።

v     በለንደን የምትኖሩ ሁላችሁም ባህላዊ ነጭ ልብሳችሁን ለብሳችሁ ኑ ብላ ቤተክርስቲያን ትጣራለች!
          ከለንደን ውጪ የምትኖሩ ደግሞ ይህን ታላቅ በአል በቅርቡ you Tube ላይ ይጠብቁ!