Saturday 24 December 2011

እነሆ የአንባቢዎች ቁጥር 1,451 ደረሰ! / Dec 25 at 8pm /

ከ1-3 በብዛት ያነበቡ ሃገሮች

uk 444
ethiopia 344
usa 285

በብዛት የተነበቡ ርዕሶች

መቆምና ማየት" 169 Pageviews
“ነገረ ማርያም  Mariology” 112  Pageviews

                                                             ወሥበሐት ለእግዚአብሔር


አሣን በጾም ለምን አንበላም?

   አሳን በተመለከተ ብዙ ግዜ ጥያቄ ይነሳል፤ በፆም አሳ ለምን አንበላም? ጌታ ለሐዋርያቱ አሳን አበርክቶ ሰቷቸዋል፤ ሐዋርያቱም አሳ በልተዋል፤ ደግሞም እኮ በድሮ ግዜ አሳ ይበላ ነበር ይህ አሁን የመጣ ታሪክ ነው ይሉና ለምን አሳን በጾም አንበላም ብለው ብዙ ግዜ ይጠይቁናል; እናንተም ተጠይቃቹ ወይም ሲባል ሰምታቹ ይሆናል። ለመሆኑ አሳን በጾም ለምን አንበላም?

የበረከት ጌታ 12ቱን እንጀራ ሁለቱን አሳና አበርክቶ 19 መሶብ ተርፎ እንደተነሳ በመጽሐፍ ተጽፎልናል። ወንጌል ዘማቴዎስ ምዕ 14/19፤ 15/34።

+++ ሐዋርያቱ አሳ በልተዋል ነገር ግን ሐዋርያቱ አሳ የበሉት መቼ ነበር? በጾም ወቅት ነበር እንዴ? አይደለም፤
ጌታ ከሐዋርያቱ ጋር እያለ መቼ ጾሙ? ሙሽራው ከነሱ ጋር እያለ አይጾሙም ሙሽራው ከነሱ የሚወሰድበት ቀን አለ ያኔ ይጾማሉ አላቸው። ማቴ 9/15 ፤ ስለዚህም ሐዋርያቱ ጾምን አልሻሩም በጾምም አሳ ስላልበሉ እኛም በጾም አሳ አንበላም ማለት ነው።

+++ ኢትብልሁ ሥጋ ዘእንበለ አሳ ይለናል በቀኖና ቤ/ተ/ክ ይህም ሥጋ አትብሉ አሳን ጭምር ማለት ነው።
ሌሎች ግን ሥጋ አትብሉ ከአሳ በቀር ብለው ተርጉመውታል ይህ ግን ልክ አይደለም። ዘእንበለ የሚለው ግዕዝ ጭምር ወይም በቀር ተብሎ ይተረጎማል። ምሳሌ እናቅርብ፦ እግዚአብሔር ፈጠረ ኩሉ አለም ዘእንበለ ትል” ሲል እግዚአብሔር አለምን ሁሉ ፈጠረ ትልን ጭምር ይባላል እንጂ ከትል በቀር አይባልም። ስለዚህም አሳን ጭምር አትብሉ ማለት ይሆናል ማለት ነው።

+++ 318ቱ ርቱሃነ ሐይማኖት አበው አባቶቻችን በጾም ክርክር ቢነሳ ለጾም አድሉ ከመብል አለመብላት እጅግ ይሻላልና ብለው አልፈዋል።

+++ በድሮ ግዜ አሳ ይበላ ነበርና አሁንም እንብላ ለሚሉ ሰዎች ድሮ አሳ ለምን እንደሚበላ ምክንያቱንም መጠየቅ አለባቸው እንጂ እንዲሁ ባጭር አረፍተ ነገር ለመብላት መዘጋጀት የለባቸውም።  በድሮ ግዜ ለኢትዮጲያ ጳጳስ የሚላከው ከግብጽ ነበር። ጳጳሳቱም ለነገስታቱ እንዲመቻቸው ብለው አሳ በጾም እንዳይበሉ ብዙም አይከለክሏቸውም ነበር፤ አንድም የግብጽ ጳጳሳት ከሃገሬው ህዝብ ጋር በሰላም ለመኖር ብቻ ስለሚያስቡ በቀኖና ላይ አልጻፉትም ነበር; ስለዚህም አሳ ይበላ ነበር፤ አሁን ግን በቅርቡ በቀኖና ቤ/ተ/ክ ስለጸደቀ አሳና ጾም ምሥራቅና ምዕራብ ናቸው; አሳ በጾም አይገባም።

+++ በጣም በቀላሉ ስናየው አሳ ሥጋ ነው ታዲያ እንዴት በጾም ይበላል? የሃገራችን ጅብ ቀን ሙሉ ይጾምና ማታ ያገኘውን ይበላል; ዋና የጾም አላማው ከጥሉላት ምግቦች በመለየት ራስን ለእግዚአብሔር ለማስገዛት ነው። ሥጋም ሆነ የወይን ጠጅ ወደ አፌ አልገባም ዳንኤል 10:3

Our Sunday School /O.S.S/
Pls Do Visit this Blog:  http:// yonas-zekarias.blogspot.com/
Our Sunday School /O.S.S/
Pls Do Visit this Blog:  http:// yonas-zekarias.blogspot.com/


አሣማ ለምን አይበላም?

+++ ሰዎች ለምን አሳማን አንበላም; በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥስ መቼ ተጻፈ እያሉ ይጠይቃሉ።
እስቲ እንጠያየቅ፤ ባስ ይዛቹ መንገድ እየሄዳቹ ነው እንበል; ከአጠገባቹ ካለው አንድ አውሮፓዊ ጋር በውይይታቹ መሃል እንዲህ ብሎ ጥያቄ ጠየቃቹ፦ ሃይማኖታቹ እጅግ ያስቀናል ግን ለምን አሳማ አትበሉም? ብሎ ጠየቀ፤ መልሳችን ምን ይሆን? ዐሳማ ርኩስ ነው ብለን ካለፍን ነጮቹ እነዚህ እኮ ኦሪታዊ ብቻ ናቸው፤ መጽሐፍ ቅዱስን አያነቡም፤ አባቶቻቸው በታሪክ ነግሯቸው እንዲሁ በዘልማድ ያመልካሉ ብለው እንደሞኝ  ይቆጥሩናል። ወርቅ የሆኑ አበው አባቶቻችን ያወረሱን ግን አንገት የማያስደፋ እውነታን ነው።

ስንመልስ እንዲህ ብለን ብንጀምር መልካም ነው፦ እኛ አሳማን የማንበልው እርኩስ ነው ብለን አይደለም። በምድር አንድም ርኩስ ነገር የለም፤ በክርስቶስ ቅዱስ ሥጋ ክቡር ደም ሁሉ ተቀድሷልና። ነገር ግን አሳማን የማንበላው በቀኖና ቤተክርስቲያን ስለተደነገገ እኛም የቤ/ተ/ክ ልጆች ስለሆንን ህጓን ለመጠበቅ ታዛዥ መሆናችንን ለመግለጽ አዎ አሳማን አንበላም እንበል። እግዚአብሔር ለአዳም በለስ አትብላ ያለውኮ በለሱ ርኩስ ስለሆነ ሳይሆን ታዛዥ የመሆኑ ምልክት ነበር።
                                     
መጽሐፍ ቅዱስስ ምን አለ

+++ አንድ ቀን ቅ/ጴጥሮስ ለመጸለይ ሰገነት ላይ ወቶ ነበር; ያኔ ከሰማይ ጴጥሮስ ሆይ ተነሳ እነዚህን አርደህ ብላ የሚል ድምጽ ሰማ፤ ጴጥሮስም ጌታ ሆይ እርኩስ ነገር በልቼ አላውቅም አለ; ያም ድምጽ እግዚአብሔር ንጹህ ያደረገውን አንተ እንደ ርኩስ አትቁጠር አለው። የሐዋ.10/9
  
ዐሳማ ሰኮናው የተሰነጠቀ ቢሆንም ስለማያመሰኳ በናንተ ዘንድ ርኩስ ይሁን። ዘሌዋውያን 11:7

ርኩስ ይሁን የተባለው ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ቅ/ሥጋውንና ክቡር ደሙን ከማፍሰሱ በፊት በኦሪት ነው። በአዲስ ኪዳን ግን ሁሉ ቅዱስ ነው; ነገር ግን ዐሳማ መብላት አለብን ማለት አይደለም። ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ ሁሉ ተፈቅዶልኛል ነገር ግን ሁሉም ነገር አይጠቅምም እንዳለ። 1ኛ ቆሮ 10:23

+++
ታንቆ የተገኘውን ወይም አውሬ የዘነጠለውን መብላት የእንስሳት ደም መጠጣት እጅግ የተከለከለ ነው ዘሌዋውያን ምዕ 17፤ በደም ውስጥ ነፍስ ስላለ የእንስሳትን ደም መጠጣት የተከለከለ ነው።
ከመ ነፍስ ዘይሃድር በደም እንደሚል

ለሚጠይቃቹ ጥያቄ ሁሉ እንዴት መልስ መመለስ እንዳለባቹ ታውቁ ዘንድ ንግግራቹ ሁል ግዜ
በጨው እንደተቀመመ በፀጋ ይሁን; ቆላስይስ 4:6

ማጠቃለያ ፦

  • አሣ በጾም አይበላም ሐዋርያቱ አሣ የበሉት በጾም ወቅት አልነበረምና

  • አሣማ የማንበላው ርኩስ ነው ብለን ሳይሆን ለቤ/ተ/ክ የፍቅር ታዛዥ መሆናችንን ለመግለጽና በቀኖና ስለተደነገገ ነው።

                                              

/ተክለ መድህን/
Our Sunday School /O.S.S/
Pls Do Visit this Blog:  http:// yonas-zekarias.blogspot.com/

Wednesday 21 December 2011

"ገድለ ሐዋርያት"


ስለ ፃድቃን ሰማእታት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በእብራዊያን መልእክቱ በተከታታይ ምዕራፍ ላይ ይናገራል።
 /እብራዊያን ምዕራፍ 11; 12 እና 13/
 

+++ እብራዊያን 11:34 አለም ለነሱ አልተገባቸውምና በየበረሀው በየዋሻው ተንከራተቱ።

ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ ጻድቃን በየበረሃው ተንከራተው እንዳለፉ ነገረን; አሁንም በሀገራችን በየገዳሙና በበረሐው ጤዛ ልሰው ዳዋ ጥሰው ዋእይ ቁሩንም ታግሰው ለሃገር ለህዝብ የሚፀልዩ አበው አሉን። ሃገራችን ብትታረስ ብዙ ጻድቃን የሚበቅሉባት ቅድስት ሃገር ናትና። መናፍቃን ግን ገዳማዊ ህይወትን ይቃወማሉ; ታላቁ ሐዋርያ ግን በመልክቱ አለም ለፃዳቃን እንዳልሆነች ነግሮናል።
+++ እብራዊያን 12:1፦ ብዙ ምስክሮች በዙሪያችን አሉን።
ሐዋርያው ሰማእታትን ምስክሮች አላቸው; ሰማ መሰከረ ሰማእትነት ምስክርነት ማለት ነው።
በእብራዊያን 11:37 ላይ እነ ነብዩ ኢሳያስ በመጋዝ ለሁለት ተሰንጥቀው ሰማእትነት እንደተቀበሉ ገለጸና እነዚህ ሁሉ ምስክሮች /ሰማእታት/ በዙሪያችን አሉ አለን።
በነፍሳቹ ዝላቹ እንዳትወድቁ የጸናውን አስቡ; እብራዊያን 12:3; ሐዋርያው የጸኑትን ሰማእታትን እንድናስብ ይመክረናል።

እብራዊያን 13:7፦ የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፤ የእምነታቸውንም ፍሬ እየተመለከታቹ በሕይወትቸው ምሰሏቸው።
 ብዙ ግዜ የወደቀውን ነው የምንመስለው ነገር ግን የጸኑትን እነ ነብዩ ኢሳያስን እነ አባ ተክለ ሐያማኖትን; ሰማእቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን መምሰል እንዳለብን ይመክረናል።

        “ገድለ ሐዋርያት”






ሐዋርያው ቅ/ጴጥሮስ




   ቁልቁል በመስቀል ላይ ተሰቀለ




ሐምሌ 5 ቀን 67 ዓ.

ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ
በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱን ተሠይፎ ዐረፈ

ሐምሌ 5

ሐዋርያው ዩሐንስ
በንጉስ ድምጥያኖስ በፍጥሞ ደሴት በፈላ ውሃ በበርሜል ውስጥ ተሰቃየ

ሞትን አልቀመሰም

ሐዋርያው በርተለሜዎስ
ከነህይወቱ አፈር በተሞላ ከረጢት ውስጥ ከተው ወደ  ባህር ወረወሩት

መስከረም 1
ሐዋርያው እንድርያስ

በግሪክ ሃገር
በ X መስቀል ላይ ተሠቅሎ ሞተ

ታህሳስ 4

ሐዋርያው ቶማስ
በጆንያ ውስጥ አፈር ሞልተው ጨው ነስንሰው መንገድ ለመንገድ ውሻ እንዲበላው አደረጉት

66ዓ:
ሐዋርያው ያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
ሄሮድስ አንቲጳስ በሠይፍ አስገደለው
በ44 ዓ.ም የሐዋ. 12:2


ሐዋርያው ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ
ከቤተ መቅደስ ጫፍ ወርውረው በድንጋይ ደብድበዉት ዐረፈ
         
            የካቲት 10

ሐዋርያው ይሁዳ /ታዴዎስ/
መጽሐፈ ሄኖክን በመጥቀሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ቁጥር 66 ብቻ አለመሆኑን አስረድቷል

  
     የይሁዳ መልዕክት  ቁ 8
ሐዋርያው ናትናኤል /ቀነናዊው ስምኦን

በሠይፍ አንገቱ ተቀላ
ሰማዕትነት ሲቀበል ሰማይ ተከፍቶ
የሥላሴን ክብር አይቷል ዩሐ. 1:51

ሐዋርያው ፊሊጶስ

በስቅላት ዐረፈ


ከዲያቆን ፊሊጶስ ይለያል የሐዋ 6:5

ሐዋርያው ማቴዎስ

አንገቱን ተሠይፎ ዐረፈ


ኢትዮጲያ መቶ ያስተማረ ሐዋርያ ነው

ሐዋርያው ማትያስ
በብረት አልጋ አስተኝተው ከስሩ ለ 7 ቀናት ያህል እሣት ለቀቁበት

በይሁዳ ምትክ የተተካ ሐዋርያው ነው

ወንጌላዊው ሉቃስ
በጆንያ አፈር ሞልተው ጨው ነስንሰው ወደ ኤዥያን ባህር ጣሉት

ወንጌልና የሐዋርያትን ሥራ ፅፏል

ወንጌላዊው ማርቆስ
በግብፅ ሃገር ከሠረገላ ጋር አስረው ቀን ሙሉ እየጎተቱት ልብሱ ተቀዶ ስጋውም እንደልብስ ተቆዶ ዐረፈ

ሚያዝያ 30

ነብዩ ኢሳያስ
ድንግል በድንግልና ትጸንሳለች ብሎ ሲተነብይ በመጋዝ ለሁለት ተሰንጥቆ ሰማእትነትን ተቀበለ

           እብራዊያን 11:34

መጥምቁ ዩሐንስ

በሔሮድስ አንገቱ በሰይፍ ተቀላ


ማቴ 14:10

ጲላጦስ ሰማእት
ከደሙ ንፁህ ነኝ ብሎ የጌታን ትንሳኤ በመመስከሩ አንገቱን በመሰየፍ ዐረፈ
Oxford Christian dictionary

ቅ/ፖሊካርፐስ

በእሣት ተቃጥሎ ሞተ

ራዕ 2:9

 ቅ/አንቲጳስ

በንጉስ ድምጥያኖስ በነሓስ መጥበሻ ተጠብሶ ሞተ

ራዕ 2:13

ቅ/ሌንጊኖስ

አንገቱን ተሠይፎ ዐረፈ
የጌታን ጎን በጦር ሲወጋ የጌታ ማየ ገቦ ሲነካው እውር የነበረ አይኑ በራ አናም አመነ

አላዛርና እህቶቹ
በቀዳዳ መርከብ ጭነው ወደ ባህር ጣሉት

በጌታ ትእዛዝ ከሞት ተነስቶ ነበር

ሊቀ ዲያቆናት ቅ/እስጢፋኖስ
በድንጋይ ተወግሮ ዐረገ

ድዳና መስማት የተሳነውን ባገኘ ግዜ እፍ እያለ ይፈውስ ነበር!!!

ቅ/ጊዮርጊስ

አንገቱን በሠይፍ ተመትሮ ዐረፈ

ሚያዝያ 23

ኢትዮጲያዊው ጃንደረባ /ባኮስ/

ወደ ጋዛ አካባቢ እያስተማረ እያለ በሠማዕትነት ዐረፈ
በአለም ለመጀመሪያ ግዜ ጥምቀትን የተጠመቀ ፤ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ሐዋርያ ነው!!!

ያስቆርቱ ይሁዳ

ለዚህ ክብር አልተገባውም





 
ሐዋርያቱ ከአንበሳ ጋር ሲታገሉ ነገሥታቱ እየተዝናኑ  የሚያዩበት ስቴዲዮም የሚመስለው ቦታ ይህን ይመስላል


ከሐዋርያቱ አንድም እድሜን ጠግቦ የሞተ የለም፤
እንዲሁ በሰማዕትነት አለፉ እንጂ!

የጻድቃን በረከት ከሃገራችን "ኢትዮጲያና ኤርትራ" አይለይ፤ አሜን!
                                                         
             
/ተክለ መድህን/