Tuesday 30 July 2013

ሹርባ ልትሰራ ሄዳ ፀጉሯን ተላጭታ መጣች



1ኛ ወደ ቆሮንቶስ ሰዎች 11

10 በዚህ ምክንያት፣ በመላዕክት ምክንያት ፣ ሴት በሥልጣን ስር መሆንዋን የሚያሳይ ምልክት በራስዋ ላይ ታድርግ። (መላዕክት ሥርዓትን ነቅተው ስለሚጠብቁ በቅዳሴ ላይ ሴቶች ፀጉራቸውን ይከናነባሉ) 

በእስራኤል ባህል አንዲት ልጅ ጸጉርዋን ካሳየች ድንግል አይደለሁም ማለትዋ ነው። የዘመናችን ሴቶች ፀጉራቸውን ፈርዘው ሲሰብኩ አይተናልና ምን እንበል? ኢስላም እንኳን ጸጉሩን ተከናንቦ ሲሄድ ኢየሱስን እንሰብካለን የሚሉ ዘመዶቻችን ምነው ልታይ ማለት ወደዱ? እንግዲህ ማንም በዚህ ጉዳይ ላይ //መከራከር// የሚፈልግ እኛም ሆነ ቤተክርስቲያን እንዲህ ያለ ልማድ የለንም። (1ኛ ቆሮንቶስ 11፦16)

ሐዋርያው ሴት ልጅ ጸጉርዋን የማትሸፍን ከሆነ ትቆረጥ ይላል። ለሴት ልጅ ፀጉርዋ ክብሯ ነው ሽልማትዋ ነው ውበትዋ ነው! ይህን የከበረ ፀጉሯን ሹርባ ልትሰራ ሄዳ ፀጉሯን ተላጭታ ከመጣች ግን ክብሯን ሽጣ መጣች ይባላል። መላጣ ሴት ከጸጉራም ሴት በክብር ትለያለች። እስኪ የሰው ክብር ልዩነቱን እንይ፦

/1/ ሁላችንም በኢየሱስ ስላመንን ቅዱሳን ነን ብላችኋል። እንግዲያውስ እኔም ከጴጥሮስ እኩል ቅዱስ ከሆንኩ እንደ ጴጥሮስ ጥላዬ በሽተኛ መፈወስ ለምን አቃተው? ዮናስ = ጴጥሮስ ለምን አልተባለም?

/2/ ወንጌላዊው ሉቃስ ስለ ማርያም ሲናገር እንዲህ አለ፦ ሁሉን በልብዋ ትጠብቀው ነበር። በልብዋ መጠበቅዋን ማን ነግሮት ይሆን? በልብዋ ትጠብቀው አትጠብቀው እንዴት አወቀ?

/3/ ጴጥሮስ ጥላው ድውይ ፈወሰ ለጳውሎስ የልብስ ቁጨት ተዓምር ሰራ ሲባል ሰምተናል። እኛስ ለምን በጥላችን በሽተኛ አንፈውስም? ባህር መክፈል ሰማይ መዝጋት ፀሐይ ማቆም ሙት ማስነሳት ለምን አቃተን?

No comments: