Monday 22 July 2013

/ /የእናት ሆድ ዥንጉርጉር እንደ ነብር ፀጉር//



ፕሮቴስታንት ዘመዶቻችን ማርያም የሰው ሁሉ እናት አትባልም ይላሉ። ክቡራን ሆይ የእናት ሆድ ዥንጉርጉር እንደ ነብር ፀጉር ሲባል አልሰማችሁም? እሺ፤ ሌላው ቢቀር የዳዊት በገናንስ አልሰማችሁም?

እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ // ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላታል።

እንግዲህ ምን እንበል? ሰው ሁሉ ጽዮን ይላታል፤ ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይላታል። መቼስ ራስን ከፍ ማድረግ የተካነ ካለ እኛም ብጹዕ ነን ማለቱ አይቀርምና እናንተ ትውልድ ሁሉ ብጹዕ አይላችሁም። ማርያም ግን ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይላታል እንላለን።

እስኪ ፕሮቴስታንት ዘመዶቻችንን እንጠይቅ፦

እምነ ጽዮን ይብል ሰብዕ ወብዕሲ ተወልደ በውስቴታ // ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላታል፤ በውስጧም ሰው ተወለደ።

/1/ ጽዮን የተባለ ሁሉ ለዳዊት ከተማ የተነገረ ነው?

/2/ ማርያምን እናታችን ስንል አኩርፋችኋል፤ ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን የሚለው የዳዊት ከተማን ነው?

/3/ በውስጧም ሰው ተወለደ ማለት ከመሬት ውስጥ ሰው ተወለደ ማለት ነው?

/4/ ትንቢተ ኢሳይያስ 60
14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል።

በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ተራራ እግርና ጫማ አለው? ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?

በተራ ቁጥር የተጻፈውን እንደ ጨዋ በየተራ እንደምትመልሱት ተስፋ አለን። ከመልሳችሁ በኋላ አስተያየትና ጥያቄ ማቅረብ መብታችሁ ነው።
...........//............

የማቴዎስ ወንጌል 26
31 እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና እነሆ በጎቹ ተበተኑ። ቅ/ማርቆስ በእምነት ያልጠነከረ ወጣት ነበረና ራቁቱን ሮጠ። እረኛው መስቀል ላይ ሲውል በጎቹ ተበተኑ። ከበጎቹ መካከል አንዱ መስቀሉ ድረስ ተከተለው። የእረኛው እናትም ከመስቀሉ ስር ነበረች።
ይቤላ ለእሙ ብእሲቶ ነዋ ወልድኪ // በመስቀል የዋለው እረኛ እናቱን እነሆ ልጅሽ አላት።
ወይቤሎ ለውእቱ ነያ እምከ // እረኛው ለበጉ እነሆ እናትህ አለው።


ይህች እናት ድንቅ ናት አምላክን ወልዳለችና። ይህች እናት ግሩም ናት የሐዋርያው እናት ተብላለችና። እንዳንቺ አይነት እናት ከቶ ማን ነው? ስለወለድሽ የሕይወት ምግብን ማርያም ሆይ እንወድሻለን! የአምላክ እናት የሐዋርያው እናት የእኛም እናት እንልሻለን።
ማርያም ለዮሐንስ ብቻ እናት ተባለች ይላሉ። ጌታ ለጴጥሮስ በጎቼን አሰማራ ሲል ለጴጥሮስ ብቻ የተነገረ ነው? ብለን ጠየቅናቸው። መልስ ግን አላገኙም። ጌታ እነሆ ልጅህ ያለውን ልጃችን አድርገን እንቀበል ይላሉ። መልሱ አዎ ልጃችሁ አድርጋችሁ መቀበል መብታችሁ ነው የሚል ነው! ማንነቱ የማይታወቀውን ልጃችን ማለት መብታችሁ ነውና። እኛ ግን ከዘፍጥረት - ራዕይ የተጻፈላትን የአምላክ እናት ማርያምን እናታችን እንላለን።
የዘመናችን ሰዎች ማርያም የሰው ሁሉ እናት አትባልም ይላሉ። ወላጅ እንደሌላቸው አልተዋችሁም ብሏልና ጌታ ረስቶ ማርያም እንዴት እናታችን ሆነች? ወይስ ማርያም የእንጀራ እናታችን ናት ይላሉ።
እኛም እንዲህ ጠየቅናቸው፤ ክርስቶስ ለዮሐንስ እነሆ እናትህ ሲል ወላጅ እንደሌላቸው አልተዋችሁም ያለውን ቃል ረስቶ ነው ወይስ ማርያም የእንጀራ እናቱ ናት? መልስ ግን ከቶ የላቸውም። መልስ የለምና አንቺው ታመጪው አንቺው ታሮጪው ብለን ዝም አልን። ሞኝ ሲናገር ብልህ ያዳምጣል እንዲሉ መናገር መልካም ነው ማዳመጥ ይበልጣል።



  • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ የማቴዎስ ወንጌል 26
    31 እረኛውን እመታለሁ የመንጋውም በጎች ይበተናሉ የሚል ተጽፎአልና እነሆ በጎቹ ተበተኑ። ቅ/ማርቆስ በእምነት ያልጠነከረ ወጣት ነበረና ራቁቱን ሮጠ። እረኛው መስቀል ላይ ሲውል በጎቹ ተበተኑ። ከበጎቹ መካከል አንዱ መስቀሉ ድረስ ተከተለው። የእረኛው እናትም ከመስቀሉ ስር ነበረች።
    ይቤላ ለእሙ ብእሲቶ ነዋ ወልድኪ // በመስቀል የዋለው እረኛ እናቱን እነሆ ልጅሽ አላት።
    ወይቤሎ ለውእቱ ነያ እምከ // እረኛው ለበጉ እነሆ እናትህ አለው።
    7 hours ago · Like · 3
  • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Solomon Girmatsion Wond Wosen/Debora Amare//Abel Tesfaye//Heaven Heaven Nahom ክቡራን ሆይ እንዴት ልታስረዱ ይቻላችኋል? ትንቢተ ኢሳይያስ 60
    14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል።

    በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ተራራ እግርና ጫማ አለው? ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?
    7 hours ago · Edited · Like · 2
  • Chirstian HaGer Nat Ethopia አሜን ቃለ ሕይወትን ያሰማልን ተባረክ ወንድሜ።
    7 hours ago via mobile · Like
  • Chirstian HaGer Nat Ethopia ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት። እግዚአብሔር ለሕዝቡ፥ በውስጥዋም ለተወለዱት አለቆችዋ በመጽሐፍ ይነግራቸዋል። በአንቺ የሚኖሩ ሁሉ ደስ እንደሚላቸው ይነግራቸዋል [መዝሙር 87:1-7]
    7 hours ago via mobile · Like
  • Yared Ashagre ወዳጄ፡ እንዲህ አይነት የአንድምታ ትምህርት ውስጥ መሳተፍ ብዙ ጊዜ ባይቀናኝም ነገር ግን ጥያቄህን እንዲሁ እንድታየው ብቻ እጽፋለሁ፡፡
    የመጽሀፍ ቅዱስን ቃላት መቼም በመደዴ እንደማትወስዳቸው ይመስለኛል፡፡ የእግዚአብሄር የእጆቹ ስራዎች ነን ሲል ቃሉ እግዚአብሄር እጅ አለው ብለህ እንደማትተረጉመው ግልጥ ነው፤ ወይም የአፍንጫው እስትንፋስ ብሎ ስለአምላክ ሲናገር አፍንጫ ያለው የፍጥረት አምሳያ እንደማትስል ይገባኛል፡፡
    ስለዚህ አንተ የማታደርገውን ሌላው እንደሚያደርገው ስለምን ታስባለህ? ወይስ ለትምህርትህ እስከተመቸ ድረስ ቃሉን የማጣጠፍ ስልጣን ያለህ ይመስልሃልን?
    በዚህ መንገድ ጥያቄህ ውድቅ ስለሆነ ሌላ መከራከሪያ ነጥብ ብታነሳ መልካም ይመስለኛል፡፡
    7 hours ago · Like · 1
  • Wond Wosen በጣም ጥሩ ይህን ካልክ የሚከተለዉስ ስለ ድንግል ማረያም ነዉ ወይንስ አይደለም!! ወንድሜ መልስ በአጭሩ እፈልጋለሁ እንዴት ፂዮን ተራራ ወይንም ቦታ እንደሆነ አስፋሀለሁ ኢሳያስ 60
    10 በቍጣዬ ቀሥፌ በፍቅሬ ምሬሻለሁና መጻተኞች ቅጥርሽን ይሠራሉ፥ ነገሥታቶቻቸውም ያገለግሉሻል።
    15 ከሰውም ማንም እስከማያልፍብሽ ድረስ የተተውሽና የተጠላሽ ነበርሽ፤ ይህ ስለማርያም ነዉ የተባለዉ ወይንስ አይደለም? አጭር መልስ እፈልጋለሁ ነዉ ወይንም አይደለም ሌላ ዝባዝንኬ አልፈልግም
    7 hours ago · Like · 2
  • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Yared Ashagre ክቡር ሆይ አሁን የሚያስከፋ ቃል መቼ ተናገርኩ? መሳተፍ ካልፈለክ ለሌሎቹ እድል መስጠት አንተም መተው መብትህ አይደለምን? ኢትዮጲያ እጆችዋን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች እጅ አላት እንዴ ብሎ መጠየቅም ይቻላል። ሆኖም ሙሉ መልስ አልሰጠህም። በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?
    7 hours ago · Like · 1
  • Wond Wosen ዮናስ መልስ ስጠኝ አትሽሽ .. በቍጣዬ ቀሥፌ በፍቅሬ ምሬሻለሁና የተባለዉ ለድንግል ነዉ
    7 hours ago · Like · 1
  • Tadesse Gebre Michael Wond Wesen,,,,,,,Zbaznke? ? ? ? Sle Maryam yemineger hulu lante " Zbaznkie" new aydel? Kkkkkkkk
    7 hours ago via mobile · Like
  • Mezgebe Alem Lisanework mejemeriya yetetekewen meles zibazinkyema atihun
  • Tadesse Gebre Michael Le Terara weym le Ketema mesgeds Le Taot ende Mesged ayhonbnm?
    6 hours ago via mobile · Like
  • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Wond Wosen ክቡር ሆይ ሰላም። በተራ ቁጥር የተጻፈውን እንደ ጨዋ በየተራ እንደምትመልሱት ተስፋ አለን። ከመልሳችሁ በኋላ አስተያየትና ጥያቄ ማቅረብ መብታችሁ ነው ያልኩትን ረሳህ? እንደ ተራህ እየመለስኩ ነው። በቍጣዬ ቀሥፌ በፍቅሬ ምሬሻለሁና ያልከው ለማርያም አይደለም። በአጭሩ መልስ ስላልክ ታዘዝኩልህ። አሁን ተራው ያንተ ነው፤ በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?
    6 hours ago · Like · 2
  • Teketel Demamu Dingay lay wuha mafises min yaderigal metewu yishalal...
  • Wond Wosen በጣም ጥሩ ስለዚህ የናቁሽ ሁሉ የሚለ ለማረያም አይደለም ማለት ነዉ! እንዲያዉም ምዕራፍ 60 የተፃፈዉ ለ ከተማዋ እንደሆነ የተረዳህ ይመስለኛል!!!ለቦታ እንደሆነ ላስረዳህ መዝሙረ ዳዊት 132 ሙሉዉን አንብበዉ 
    5 ለእግዚአብሔር ስፍራ፥ ለያዕቆብ አምላክ ማደሪያ እስካገኝ ድረስ ብሎ። ይልና እ/ር ደግሞ እንዲህ ይላል
    13 እግዚአብሔር ጽዮንን መርጦአታልና፥ ማደሪያውም ትሆነው ዘንድ ወድዶአታልና፥ እንዲህ ብሎ።
    14 ይህች ለዘላለም ማረፊያዬ ናት፤ መርጫታለሁና በዚህች አድራለሁ።
    15 አሮጊቶችዋን እጅግ እባርካለሁ፥ ድሆችዋንም እንጀራ አጠግባለሁ።
    16 ካህናቶችዋንም ደኅንነትን አለብሳቸዋለሁ፥ ቅዱሳኖችዋም እጅግ ደስ ይላቸዋል።
    17 በዚያ ለዳዊት ቀንድን አበቅላለሁ፥ ለቀባሁትም ሰው መብራትን አዘጋጃለሁ።
    18 ጠላቶችንም እፍረትን አለብሳቸዋለሁ፤ በእርሱ ግን ቅድስናዬ ያብባል። ይህ ማለት የዳዊትን ከተማ ፂዮንን ስለመሆኑ አትጠራጠር!! ዳዊት የፀለየዉ ጸሎት እ/ርን ለማሳረፍ ስለነበረ ፀሎቱ ተሰምቶለት የዳትን ከተማ መረጸ በመካከላቸዉ አደረ!! ይህን ለድንግል ማርያም መስጠት ወደስህተት ይወስዳልና በደንብ አጢነዉ!! ልታዉቅ የሚገባህ በብሉይ ኪዳን አይሁድና ሳምራዊ የሚሰግዱበት ቦታ የተለያየ እንደሆነ የምትአነጋ አይመስለኝም ለዛም ነዉ ወደ ፂዮን ይመጣሉ ስግደትንም ይፈፅማሉ! ለማለተ ነዉ! ለተራራ መስገድ ሳይሆን በተራራዉ ላይ በከተማዉ ላይ ስግደት ለእ/ር ማቅረብ ማለት ነዉ!! ደግሞ ስግደት የሚያስፈልገዉ ለእ/ር ብቻ እንደሆነ መዘንጋት የለብህም!!
  • Tadesse Gebre Michael @ Ol Pro's,,,,,,,,,,,,,,"Yenakushm wede Egrsh chama ysegdalu". Mn malet yhon ? Ewnet ye E/r kal le Terara weym le Ketema endnsegd ynageral? Bnsegds le Taot endemesged ayhonbnmn?kehone tadya lemanew yetetsafew?
    6 hours ago via mobile · Unlike · 1
  • Yared Ashagre ለተራራ መስገድ ጣኦት አምልኮ ነው፤ እንዲሁም ለፍጥረት መስገድ፡፡ ለጌታ ለአምላክህ ስገድ፤ እርሱንም ብቻ አምልክ ብሎ ጌታ ሰይጣንን ያባረረው በዚህ እውነት ላይ ቆሞ ነው፡፡ አለቀ፡፡ 
    አንድ የመጽሀፍ ክፍል ቁጥርን ገንጥሎ በዚያ ላይ መነጋገር አውድን ማጥፋት በሚባል ወንጀል ውስጥ ይከትታል፡፡ ይህንንም ብዙ ጊዜ ጥራዝ ነጠቅ እያላችሁ ሌሎችን ለመሳደብ እንደመንደርደሪያ ስትጠቀሙ ይስተዋላል፡፡ ያንኑ ወንጀል ደግሞ እናንተው ስታደርጉት አይታያችሁም፡፡
    የኢሳይያስ 60 ከተማ የራእይ 21 አዲሲቷ ኢየሩሳሌም መሆኗን በንጽጽር ቃል በቃል ማየት ይቻላል፡፡
    ስለዚህ ያለምንም ሌላ ማብራሪያ ሁለቱን ክፍሎች ማንበብ በቂ ነው፡፡
  • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Wond Wosen ክቡር ሆይ ለከተማዋ መሆኑን ስላስረዳኸኝ አመሰግናለሁ። ሆኖም የጠየኩትን ከመለስክ በኋላ ብታስረዳን ደስ ይለን ነበር። /1/ ጽዮን የተባለ ሁሉ ለዳዊት ከተማ የተነገረ ነው? /2/ በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?
    6 hours ago · Edited · Like · 1
  • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Yared Ashagre ክቡር ሆይ የመለስኩት በቂ ነው ብለሃልና አመሰግናለሁ።
  • Chirstian HaGer Nat Ethopia ወንደሰን ለምን ትቆራርጠዋለህ ማደርያ እስካገኝ ብሎ ይላል አልክ በጣም ጥሩ አሁን ለምጠይቅ መልስ እፈልጋለው በመጀመርያ ሙሉውን ፖስት አድርገው?
    6 hours ago via mobile · Like
  • Chirstian HaGer Nat Ethopia ከክብሩ ውበት ከጽዮን እግዚአብሔር ግልጥ ሆኖ ይመጣል።[መዝ 50:2] በጽዮን ለሚኖር ለእግዚአብሔር ዘምሩ፥ በአሕዛብም መካከል አደራረጉን ንገሩ::[መዝ 9:11] ከኃይል ወደ ኃይል ይሄዳሉ፤ የአማልክት አምላክ በጽዮን ይታያል። [መዝ 84:7]
    6 hours ago via mobile · Unlike · 1
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ ክቡራን ፕሮቴስታንት ዘመዶቻችን ሆይ ምን ትላላችሁ? 
      1/ ጽዮን የተባለ ሁሉ ለዳዊት ከተማ የተነገረ ነው?

      /2/ ማርያምን እናታችን ስንል አኩርፋችኋል፤ ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን የሚለው የዳዊት ከተማን ነው?

      /3/ በውስጧም ሰው ተወለደ ማለት ከመሬት ውስጥ ሰው ተወለደ ማለት ነው?

      /4/ ትንቢተ ኢሳይያስ 60
      14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል።
      6 hours ago · Like · 2
    • Wond Wosen ዮናስ.. ያልገባህ ነገር ያለ ይመስለኛል! በሐዋርያት ስራ ኢትዮጺያዊዊ ጃንደረባ ወደ ኢየሩሳሌም ሊሰግድ የሄደዉ ለምን ይመስልሀል! ለቦታዉ ነዉ ወይንስ የእ/ር ታቦት መገኛ ስለሆነ? ማንም ለተራራ አይሰግድም ነገር ግን የሚሰግዱበት ቦታ ፂዮን ይባላል ከተማ ወይንም ተራራ ሊሆን ይችላል ነገር ግን ስግደት ለእ/ር ነዉ! አይሁድንም ብትጠይቃቸዉ የሚመልሱልህ መልስ ይህ ነዉ!!!
      6 hours ago · Like · 1
    • Tadesse Gebre Michael Yared,,,,,,,,,,,yetenadedk tmeslaleh. Manm yasgededeh akal ko yelem.
      6 hours ago via mobile · Like
    • Mezgebe Alem Lisanework hahahhahaha wond , i think you failed
    • Chirstian HaGer Nat Ethopia እኔ ምለው ግን ባይብልን ገልብጣችሁ ነው ምታነቡት ግን?
      6 hours ago via mobile · Edited · Like
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Wond Wosen ወንድሜ ወንደሰን ኢሳይያስ የሚያወራው ስለማን ነው? ስለ እግዚአብሔር ነው ወይስ ስለ ጽዮን? ትንቢተ ኢሳይያስ 60
      14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል።
    • Weyni Getachew mels ayisetuhm wegeyachew ki kidest dingel Maryam ga selehone,,,,,
    • Yared Ashagre • አሕዛብም ወደ ብርሃንሽ ነገሥታትም ወደ መውጫሽ ጸዳል ይመጣሉ። . . . . . . ኢሳ 60
      አሕዛብም በብርሃንዋ ይመላለሳሉ፥ የምድርም ነገሥታት ክብራቸውን ወደ እርስዋ ያመጣሉ፤. . . . ራእ 21፡24
      • በዚያን ጊዜ የባሕሩ በረከት ወደ አንቺ ስለሚመለስ፥ የአሕዛብም ብልጥግና ወደ አንቺ ስለሚመጣ፥ አይተሽ ደስ ይልሻል፥ ልብሽም ይደነቃል ይሰፋማል። ኢሳ 60
      የአሕዛብንም ግርማና ክብር ወደ እርስዋ ያመጣሉ። ራእይ 21፡ 26
      • በሮችሽም ሁልጊዜ ይከፈታሉ ሰዎች የአሕዛብን ብልጥግና የተማረኩትንም ነገሥታቶቻቸውን ወደ አንቺ ያመጡ ዘንድ ሌሊትና ቀን አይዘጉም። ኢሳ 60

      የምድርም ነገሥታት ክብራቸውን ወደ እርስዋ ያመጣሉ፤ በዚያም ሌሊት ስለሌለ ደጆችዋ በቀን ከቶ አይዘጉም፥ ራእይ 21፡ 24-25
      • ከዚያ በኋላ እግዚአብሔር የዘላለም ብርሃንሽ፥ አምላክሽም ክብርሽ ይሆናልና ፀሐይ በቀን ብርሃን አይሆንልሽም፥ የጨረቃም ብርሃን በሌሊት አይበራልሽም። ኢሳ 60

      ለከተማይቱም የእግዚአብሔር ክብር ስለሚያበራላት መብራትዋም በጉ ስለ ሆነ፥ ፀሐይ ወይም ጨረቃ እንዲያበሩላት አያስፈልጓትም ነበር። ራእ 21፡23
      እና የመሳሰሉትን አንድ አይነት አሳቦች ሁለቱም ስፍራዎች እናገኛለን፡፡ አዲሲቷ ኢየሩሳሌም፤ የንጉሱ ከተማ፤ የክርስቶስ ኢየሱስ አካል የሆነችው ቤተክርስቲያን እውነት በራእይ ላይም ሆነ በኢሳይያስ ትንቢት ላይ ቁልጭ ብላ ትታያለች፡፡
    • Tadesse Gebre Michael Yared,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,," Ye nakushm Hulu wede Egrsh Chama ysegdalu" yemilewns alagegnehewm ende? Slemn tewkew?
      6 hours ago via mobile · Like · 1
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ ብዙ ማብራሪያ ተሰጥቶናልና ማመስገን ይገባናል። ሆኖም መልሱን የሚመልስ ማን ነው? 1/ ጽዮን የተባለ ሁሉ ለዳዊት ከተማ የተነገረ ነው?

      /4/ ትንቢተ ኢሳይያስ 60
      14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?
      6 hours ago · Like · 3
    • Tadesse Gebre Michael Betekrstyan snsalem na le E/rs bihon snsegd enante aydelem ende, le Dingay mesalem mn malet new? Eyalachu Orthodoxawyann yemttechut? Endet zare sle Betekrstyan tekorekorachu?
      6 hours ago via mobile · Like
    • Chirstian HaGer Nat Ethopia በጣም እኮ ነው ሚገረመው ለተጠየቁት መልስ ሳይዙ አሰስ ገሰሱን ከየት ይጠይቃሉ ከየት እንደሚያመጡት ብቻ ነው ገርም ሚለኝ
      6 hours ago via mobile · Like
    • Yared Ashagre Tadesse Gebre Michael: No my friend; I didn't drop that:

      Isa 60:14 And the sons of them that afflicted thee shall come bending unto thee; and all they that despised thee shall bow themselves down at the soles of thy feet; and they shall call thee The city of Jehovah, The Zion of the Holy One of Israel. 

      Yeah, the Church is well afflicted by the Jews and the world, and I hope you read the history of Nero the burner who put ablaze many Christians in fire. These are some of the afflictions the Church passed through. Despised? Yes the Church was well despised by the Greeks and the intellectuals of the time, and even in our recent history, the Church has been labeled as irrelevant and improper to modernism. 
      And look at Hebrews 12: 

      ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፥
      በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፥ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች፥
      የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።
      ነገር ግን ወደ ጽዮን ተራራና ወደ ሕያው እግዚአብሔር ከተማ ደርሳችኋል፥ ወደ ሰማያዊቱም ኢየሩሳሌም፥ በደስታም ወደ ተሰበሰቡት ወደ አእላፋት መላእክት፥
      በሰማያትም ወደ ተጻፉ ወደ በኵራት ማኅበር፥ የሁሉም ዳኛ ወደሚሆን ወደ እግዚአብሔር፥ ፍጹማንም ወደ ሆኑት ወደ ጻድቃን መንፈሶች፥
      የአዲስም ኪዳን መካከለኛ ወደሚሆን ወደ ኢየሱስ፥ ከአቤልም ደም ይልቅ የሚሻለውን ወደሚናገር ወደ መርጨት ደም ደርሳችኋል።
    • Bright Destiny Yared Ashagre can you pls tell us why did you write the verse 60:14 in English and the rest in Amharic ?
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ ለማብራሪያው በድጋሚ እናመሰግናለን። መልሱን የሚመልስ ግን ማን ነው?
    • Tadesse Gebre Michael Lemamtatat newa!
      6 hours ago via mobile · Like
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ ልበ አምላክ ዳዊት በገናውን እየደረደረ እንዲህ አለ፦
      እምነ ጽዮን ይብል ሰብእ /ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላታል፤ በውስጧም ሰው ተወለደ! / መዝ [86: 5]
      ከመሬት ውስጥ ሰው ይወለዳል እንዴ? አይወለድም ወደፊትም አይወለድም፤ መዝሙሩን ልብ ብለን ስናነበው ግን “ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላታል፤ በውስጧም ሰው ተወለደ!” ይላል፤ ስለዚህም ጽዮን የተባለችው እመቤታችን ናት። የዳዊት በገና ቀጠለ እንዲህም አለ፦ እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፤ ይህች ለዘለዓለም ማረፊያዬ ናት፤/ዛቲ ይዕቲ ምዕራፍየ ለአለም/ መርጫታለሁና በእርሷም አድራለሁ። መዝ [131: 13]
      5 hours ago · Like · 4
    • Yared Ashagre በጣም አስቂኝ ድምዳሜ ነው፡፡ ባራክ ኦባማ አሜሪካ ውስጥ ተወለደ ማለት የአሜሪካ መሬት ወለደው ማለት ነውን? በፍጹም! ይህንን መቼም ማብራራት አያስፈልገውም ነበር፡፡
    • Feker Tsige mekawem bicha lela min alachew protestantochi
      5 hours ago via mobile · Unlike · 1
    • እንዳለልኝ አበራ ቾንቤ YARED@ TERO KALEDAGNA NAHE MAZEMUR 86:5 SAWE HOLO EINATACHEN TEYONE YELATELE BAWESTA SAWE TAWELDALEN= YEHA TENEBETE NAWE MAJAMREYA YATENAGERAWE LA NEGOSE DAWETE NAWE FETAMEWE LA EIYASOSE KERESTOSE YATENAGER NAWE SELAZEHE TEYONE YETEBALCHAWE DENGELE MAREYAMENE SETEHONE SAWE YTEWELDAWE EIYASOSE KERESTOSE NAWE LAZEHE YAMEYAREGAGETELHE BA EISAYASE 59:20 YALAWEN KALE BADANEBE ANEBEBAWE
      5 hours ago via mobile · Edited · Unlike · 2
    • DM HI Yared Ashagre Anyone who tries to deal in a logical manner with an illogical person is on a fool's errand.
    • Wond Wosen Mezgebe Alem Lisanework why i failed
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Yared Ashagre በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም? መልሱ ይለፈኝ አላችሁ? // ባራክ ኦባማ አሜሪካ ውስጥ ተወለደ ማለት የአሜሪካ መሬት ወለደው ማለት ነውን? ብላችሁ መጠየቅ ያለባችሁ ራሳችሁን ነበር። /1/ /ሰው ሁሉ እናታችን ጽዮን ይላታል፤ በውስጧም ሰው ተወለደ! / መዝ [86: 5] ማለት ምን ማለት ነው? /2/ እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፤ ይህች ((ለዘለዓለም ማረፊያዬ ናት)) ማለትስ ምን ማለት ይሆን?
    • Yared Ashagre Endalelign Abera: ለዳዊት የተነገረ ጊዜ የትንቢቱ የመጀመሪያ ፍጻሜ ነበር ብለሃል ወዳጄ፡፡ የክርስቶስ ጊዜ ማርያም ከሆነች የዳዊት ጊዜ ያኔ ታዲያ ጽዮን ማን ነበረች?
    • Tadesse Gebre Michael Mezmur 86:5,,,,,,, Mann yhon ahuns Tsyon enatachn yemnlew? Dawit keteman? Tsyon Teraran? Weys Tsyon Maryam?
      5 hours ago via mobile · Unlike · 1
    • Yared Ashagre Yoni Ab: Yonas Zekariyas: ለአንተ አተረጓጎም የተሰጠ መልስ ነበር እኮ ወዳጄ፡፡ ሰው መሬት ውስጥ ይወለዳል ወይ ብለህ የወሰድከው ድምዳሜ መሬት ውስጥ ካልተወለደ እንግዲያውስ. . . .የሚል ነበር፡፡ እንግዲህ ሰው ስለአገሩ ተናግሮ በዚያ ተወለድኩ ሲል የአገሪቱ መሬት ውስጥ ተወለድኩ ማለቱ ነው ወይስ ደግሞ ስፍራን እያመላከተ ነው? ነበር ጥያቄያዊ ምላሼ፡፡ አንተ ደግሞ ወደእኔው አዞርከው፡፡
    • እንዳለልኝ አበራ ቾንቤ MAJAMREYA SELAKTEMAWE SELA ANEBAYETO TEYONE YATENAGER nawe
      5 hours ago via mobile · Edited · Like
    • Yared Ashagre የሚያውቁኝን ረዓብንና ባቢሎንን አስባቸዋለሁ እነሆ፥ ፍልስጥኤማውያን ጢሮስም የኢትዮጵያም ሕዝብ፥ እነዚህ በዚያ ተወለዱ።
      ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት።

      ከጽዮን ተጨማሪ ረዓብ፤ ባቢሎን፤ ፍልስጥኤም፤ ጢሮስና ኢትዮጵያ ተጠቅሰዋል፤ እነዚህስ እነማን ናቸው?
    • Mati Mat ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ - የመናፍቃን ትልቁ ማሳሳቻ ግማሽ መጥቀስ ነው. ሰይጣን ጌታን ሲፈትነው የነበረው ግማሽ በመጥቀስ ነበር. ሙሉው ጥቅስ መዝ86-5 "ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት" "This and that man was born in her: and the highest himself shall establish her." ልኡል መሰረታት የተባለው በውስጧ ሰው የተወለደውን ወንድሜ ማሪያም ናት ያላትን ነው. ማሪያም ተፈጠረች ወይስ ተመሰረተች? እ/ር ሰውን በመልካችንና እንደምሳሌአችን እንመስርት አለ እንዴ ? የሚመሰረተው /establish ሰው ነው ወይስ ከተማ ?ሰው የሚወለደው ከውስጥ ወደ ውጭ ወይስ ከውስጥ ወደ ውስጥ ? ይህንን መልስልኝ
    • Mati Mat ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ መዝ 86-6 "እግዚአብሔር ለሕዝቡ፥ በውስጥዋም ለተወለዱት አለቆችዋ በመጽሐፍ ይነግራቸዋል።"ለመሆኑ በመጽሃፍ የሚነግራቸው በውስጧ የተወለዱት አለቆች ስንት ናቸው?ማሪያም ብዙ አለቆችን ወልዳለችን?
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Mati Mat ሰላም ወንድም ዓለም። ሁል ጊዜ ከመልስ በኋላ ጥያቄና ማብራሪያ ብናስከትል መልካም ነበር። " ልኡል መሰረታት ማደሪያው ትሆን ዘንድ ቀደሳት ሰራት አመቻችቶ በንጽህና በቅድስና መሰረታት ማለት ነው። ልኡል ማደሪያውን ቀደሰ እንዲል። 1/ ጽዮን የተባለ ሁሉ ለዳዊት ከተማ የተነገረ ነው?

      /4/ ትንቢተ ኢሳይያስ 60
      14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?
      about an hour ago · Like · 3
    • Wond Wosen መልስ ተሰጠህ እኮ አንብበህ ችግር ያለበት ቦታ ያልገባህ ካለ ንገር ጽዮን የተራራ ስም ነዉ! አንተ ለማርያም ይሰግዳሉ ለማለት ፈልገህ ነዉ! እንዲያ ከሆነ በዕዉነት ሞኝ ነህ!! ብሉይን በደንብ አንብብ
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Wond Wosen ወንድም ዓለም ምክራችሁ በዛ፤ መልሱን ግን ማን ይመልስ ?በዚህ ትንቢት ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?
      4 hours ago · Like · 1
    • Mati Mat ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ-1/ ጽዮን የተባለ ሁሉ ለዳዊት ከተማ የተነገረ ነው? ላልከው እያወራን ያለነው ስለ ኢሳ60-14 ስለሆነ እሱን ጨርሰን አንድ በአንድ ማየት ይቻላል. "ጌታ ኢየሱስ እናንተ ሸክማችሁ የከበደ ደካሞች ወደእኔ ኑ ..." እንዲሁም " ...ህይወት እንዲሆንላችሁ ወደእኔ መምጣት አትወዱም" የሚሉት ተሰርዞ "ወደእናቴ ሂዱና ወደእግሯ ጫማ ስገዱላት" የሚል ጌታ የለንም. "ጽዮን የተባለችው የዳዊት ከተማ ከሆነች ለተራራ መስገድ ጣዖት አይደለም?" ላልከው ጌታ ለሳምራዊቷ ሴት " በዚህ ተራራ ወይም በኢየሩሳሌም የማትሰግዱበት ግዜ ይመጣል..." ሲል ለተራራውና ለከተማው የማትሰግዱበት ...ማለቱ አልነበረም. ይልቁንስ በእውነትና በመንፈስ ስለመስገድ ሲያስተምር እንጂ በኢየሩሳሌምም ሆነ በተራራው የሚሰግዱትና የሚሰውት ለእ/ር እንደሆነ ያውቃል.
      4 hours ago · Like · 1
    • Wond Wosen በዚያ የእ/ር ክብር አለ! አንድ ጥያቄ ልጠይቅህ ኢትዮጺያዊዉ ጃንደረባ ወደ ኢየሩሳሌም የሄደዉ ለምንድን ነዉ ሐዋ 8 
      27 ተነሥቶም ሄደ። እነሆም፥ ህንደኬ የተባለች የኢትዮጵያ ንግሥት አዛዥና ጃንደረባ የነበረ በገንዘብዋም ሁሉ የሠለጠነ አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር፤ ለኢየሩሳሌም መስገድ ጣኦት አየደለምን? በአንተ አባባል? የኔ ወንድም ጽዮን ተራራ ስለመሆኗ አትከራከር በዚያም ለመስገድ መሄድ የእ/ር ክብር ያለበት ቦታ ስለሆነ እንጂ አንተ እንደምታሰበዉ አይደለም! ዉስጥህ እያወቀዉ ነዉ!!!!!!
      4 hours ago · Like · 2
    • Yared Ashagre Isa 60
      14 The sons also of them that afflicted thee shall come bending unto thee; and all they that despised thee shall bow themselves down at the soles of thy feet; and they shall call thee, The city of the Lord, The Zion of the Holy One of Israel.

      ወዳጄ ዮናስ፡ አንተ ሙሉ አሳቡን በጥንቃቄ ብታነብበው መልስህንም እዚያው ስለምታገኘው አትጠይቅም ነበር፡፡ ያንተ ጥያቄ ያው ጽዮን ማርያም ናት ለማለት መንደርደሪያ እንደሆነ ግልጥ ነው፡፡ እኛ ደግሞ ስንመልስልህ ጽዮንን ማርያም እንዳይደለች ለማሳየት ከሚል ልብ ተነስተን ሳይሆን ቃሉን በትክክል ከመገንዘብ ተነስተን ነው፡፡
      ስለዚህም ለተራራም ሆነ ለፍጥረት መስገድ ትክክል አይደለም፤ ነገር ግን እዚህ ጋር እያወራ ያለው ስለጽዮን አገዛዝ ከሁሉ በላይ ሆና የእግዚአብሄር ከተማ ተብላ ከፍከፍ ስለማለቷ፤ ነገስታትንና ባለጠጎችን ሁሉ ስለማንበርከኳ ነው፡፡ ይህ ደግሞ በራእይ 21 ላይ በግልጥ አዲሲቷ ኢየሩሳሌም የንጉሱ ከተማ እንደሆነች ማስተዋል እንችላለን፡፡
      ስለዚህ ለተራራ መስገድ ጣኦት ሆኖ ሳለ የጽዮን ገዢ ታላቅ ከመሆኑ የተነሳ ሁሉ ለእርሷ መንበርከካቸው ግን አምልኮን ወይም ሌላን ነገር አያሳይም፤ ይልቁን የንጉሱን ታላቅነት እንጂ፡፡
      አሜሪካ ልእለ-ሀያል አገር ተብላ አገሮች ሁሉ ሰገዱላት ሲባል አመለኳት ማለት አይደለም፤ ይልቁን አስገበረች፤ አንበረከከች፤ ገዛች. . .ወ.ዘ.ተ ማለት ነው፡፡
      አድካሚ ዙር ለምን እንደምትሄድ አይገባኝም፡፡
      4 hours ago · Like · 2
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Mati Mat ወንድም ዓለም አሁን ከሌሎቹ አንድም ከሌላው ቀንም የተሻለ መልሰሃልና አመሰግናለሁ። በኢየሩሳሌምም ሆነ በተራራው የሚሰግዱትና የሚሰውት ለእ/ር እንደሆነ ያውቃል. ብለኸናል። ትንቢተ ኢሳይያስ 60
      14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። ኢሳይያስ የሚያወራው ስለ ጽዮን ነው ወይስ ስለ እግዚአብሔር? ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የተባለው ለእግዚአብሔር ነው?
      4 hours ago · Like · 3
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ ወንድም ዓለም Wond Wosen አንድ የኢትዮጵያ ሰው ሊሰግድ ወደ ኢየሩሳሌም መጥቶ ነበር፤ለኢየሩሳሌም መስገድ ጣኦት አየደለምን? ብለሃል። በኢየሩሳሌም መስገድና ለኢየሩሳሌም መስገድ በጣም ይለያያሉ።
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ እግዚአብሔር ጽዮንን መርጧታልና፤ ይህች ((ለዘለዓለም)) ማረፊያዬ ናት፤/ዛቲ ይዕቲ ምዕራፍየ ለአለም/ መርጫታለሁና በእርሷም አድራለሁ። መዝ [131: 13] በዚህ ጥቅስ ጽዮን የተባለችው ከተማ ናት የሚሉ አሉ። የዳዊት ከተማ ለዘለዓለም ማረፊያው ናት?
    • Tadesse Gebre Michael Ol Pro's,,,,,,,,,,,,,,Le tsyon terara mesged yaltegeba aydelemn? Le Dawit ketemas mesged le Taot endemesged aydelemn? Tadya enezi hulu kentu dkam kehone"wede egrsh chama ysegdalu"yetebalew lemn yhonal? Meches sle Maryam sinegerachu yemaywat slemihonbachu enji Glts new.
      4 hours ago via mobile · Like
    • Tadesse Gebre Michael Ye Dawit ketemas zelealemawi nat? Le Zelalem marefyaye endthon merchatalehu ylal na?
      4 hours ago via mobile · Like
    • Tadesse Gebre Michael Yared & Mati,,,,,,,,,,,,and aquam meyaz alebachu. TSYON yemilew le Dawit ketema new weys le Semayawit Eyerusalem?
      4 hours ago via mobile · Like
    • Tadesse Gebre Michael Le Maryam yemilew legizew ykrbachu. Be huletum zurya new yalachut na.
      3 hours ago via mobile · Like
    • Mati Mat ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ/Tadesse Gebre Michael-ኢሳ52-1 " ምርኮኛይቱ የጽዮን ልጅ ሆይ፥ የአንገትሽን እስራት ፍቺ" ስለሚል ሰው እንጂ ተራራ አንገት ስለሌለው ማሪያም ምርኮኛ ሴት ልጅ አላት ማለት ነው? ስለዚህ ማሪያም ልጅ አላት የሚለውን ትደግፋላችሁ ማለት ነው.?
    • Tadesse Gebre Michael Yhn r'es lela gizie wendme.
      3 hours ago via mobile · Like
    • Mati Mat Tadesse Gebre Michael -ምነው ከኢሳ60-14 ጋር የተያያዘ ነው እኮ
    • Mati Mat መልሱን የሚመልስ ግን ማን ነው?
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Mati Mat Heaven Nahom አላዋቂ ሰው ብዙ እየተናገረ አለማወቄን እወቁልኝ ይላል። ኢትዮጲያ እጆቿን ወደ እግዚአብሔር ትዘረጋለች ማለት እጅ አላት ማለት ነው? አንተ የጠቀስከው ስለ ዳዊት ከተማ ነው። ከላይ የጠየኩህን ለመመለስ ሞክር፦ ትንቢተ ኢሳይያስ 60
      14 የአስጨናቂዎችሽም ልጆች አንገታቸውን ደፍተው ወደ አንቺ ይመጣሉ፥ የናቁሽም ሁሉ ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የእግዚአብሔርም ከተማ፥ የእስራኤል ቅዱስ የሆንሽ ጽዮን ይሉሻል። ኢሳይያስ የሚያወራው ስለ ጽዮን ነው ወይስ ስለ እግዚአብሔር? ወደ ((እግርሽ ጫማ )) ((ይሰግዳሉ )) የተባለው ለእግዚአብሔር ነው?
      40 minutes ago · Like · 3
    • Tadesse Gebre Michael Tyake be tyake memeles tejemere ende? Ante mn tlaleh? Eshi Ethiopia ej alat ltlen yhon? Mezmur 67
      3 hours ago via mobile · Edited · Like
    • Mati Mat ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ /Tadesse Gebre Michael. ሙሉው ጥቅስ መዝ86-5 "ሰው እናታችን ጽዮን ይላል፥ በውስጥዋም ሰው ተወለደ፤ እርሱ ራሱም ልዑል መሠረታት" "This and that man was born in her: and the highest himself shall establish her." ልኡል መሰረታት የተባለው በውስጧ ሰው የተወለደውን ወንድሜ ማሪያም ናት ያላትን ነው. ማሪያም ተፈጠረች ወይስ ተመሰረተች? እ/ር ሰውን በመልካችንና እንደምሳሌአችን እንመስርት አለ እንዴ ? የሚመሰረተው /establish ሰው ነው ወይስ ከተማ ?ሰው የሚወለደው ከውስጥ ወደ ውጭ ወይስ ከውስጥ ወደ ውስጥ ? ይህንን መልሱልኝ

    • 2 hours ago · Edited · Like · 2
    • ዲያቆን ዮናስ ዘካርያስ Yegeta Meseker ከመልሱ አንድ ነገር እንድትረዱ ስለፈለኩ ነው። ፕሮቴስታንትም መልስ አላት ለማለት ሞክሩና ጥያቄውን ሞክሩት
    • Tadesse Gebre Michael Tyake, weym lela asteyayet kalachu mels kesetachu bewhala endemitebeklachu Bemasaseb neber tyakewn post yetederegew.
      2 hours ago via mobile · Unlike · 1
    • Shimelis Mergia Mati Mat ወይስ ዘንዶው ከተቆጣባት ከሴቲቱ ና ከዘርዋ ከቀሩት የክርስቶስ ምስክርነት ካላቸው ወገን ነህን? ከዘርዋ ከክርስቶስ ወገን ከሆንክ የሴቲቱ ልጅ ነህ ማለት ነውና፡፡
      2 hours ago · Like · 3
    • Mati Mat Shimelis Mergia- አንድ ነገር ላስረዳህ."የክርስቶስ ምስክርነት ካላቸው " የሚለውን ስትሰማ ምን ታስታውሳለህ? "ስለእኔ በሰዎች ሁሉ ፊት የሚመሰክርልኝ እኔም በአባቴ ፊት እመሰክርለታለሁ" ምን ብሎ የመሰከረ ?"ኢየሱስ ጌታ እንደሆነ በአፍህ ብትመሰክር..." አይልም? ስለእናቱ ይላል? ስለመላእክት ይላል ?ስለቅዱሳን ይላል. ?አሁን የክርስቶስ ወገን ማን እንደሆነ ይገባሃል
    • Shimelis Mergia Mati Mat ምንድን ነው ግን እንዲህ ዘንዶው በተቆጣበት “በሴቲቱ” ላይ እንዲህ በጠላትነት መነሣትህ? ይህቺ እኮ የክርስቶስ ምስክርነት ላላቸው ሁሉ እናት ናት ምንክያቱም በክርስቶስ የእርሱዋ ዘሮች ተብለዋልና፡፡
      2 hours ago · Edited · Like · 4
    • እንዳለልኝ አበራ ቾንቤ MATI@ KA ZANEDWE GARE TELE YALETE SETETO NATE SATETO DAGEM DENGELE MARYAMENE NATE = KA MALEKTO GARE YATETALAWE ZANDWE NAWE TADEYA YASO AGAFERE NAHE ? WAYES KA WEDEYETEGNAWE WAGANE NAHE
      2 hours ago via mobile · Like · 1
    • Shimelis Mergia Mati Mat “ስለክርስቶስ በመመስከር” ሴቲቱን ትቀድማት ይሆን? ነፍሴ ጌታ ታከብራለች መንፈሴም በአምላኬና በመድኀኒቴ ሐሴትን ታደርጋለች …. በእኔ ታላቅ ሥራን አድረጋጓልና ትውልድ ሁሉ ብጽዕት ይሉኛል" ያለች የአምላክ እናት ናት፡፡ እንደ እርሱዋ ከነፍሳቸው ጥግ ክርስቶስን የሚያመልኩ ሁሉ ስለክርስቶስ የሚመሰክሩ ናቸው፡፡ እነርሱም የእርሱዋ ዘሮች ይባላሉ፡፡ መጽሐፍ ይህን አረጋግጦልናል፡፡
      2 hours ago · Like · 3
    • Tadesse Gebre Michael Mati,,,,,,,,,,,,Tifozo neh?
      2 hours ago via mobile · Like
    • Tadesse Gebre Michael Mati,,,,,,,,,,,,Tifozo neh?
      2 hours ago via mobile · Like
    • Wond Wosen Tadesse Gebre Michael yeman tifozo.. ye arsenal woynis ye chealse??
    • Tadesse Gebre Michael Wond wosen,,,,,,,,,,,,Ye tnte telatachn
      2 hours ago via mobile · Like · 1
    • እንዳለልኝ አበራ ቾንቤ WAND WANSNE@ ANETASE YA ZANDAWE TABABRE NAHE? MIKENEYATOME ZANEDOWE YATETALWE KA SETETO GARE EINA KA MALEKETO GARE NAWE ANETE KAYATEGNAWE WAGANE NAHE ?
      2 hours ago via mobile · Like · 1
    • Dereje Shibru ***** kale hiwot yasemalin yagelgilot zemenih yetebareke yhun amen.
      about an hour ago via mobile · Like · 1

No comments: