Saturday 26 November 2011

በእንተ “ስማ ለማርያም”

            በእንተ “ስማ ለማርያም”


+++ መፅሐፍ ቅዱስ እንዲህ ይላል፦ ፀሐይን ተጎናጽፋ ጨረቃንም ተጫምታ በራስዋ ላይ 12 ከዋክብት ያለበት አክሊል የተቀናጀች አንዲት ሴት ነበረች ራዕይ 12:1; የእመቤታችን ክብር እንዲህ ይነበባል። እስቲ እያንዳንዱን ቃል በቃል እንየው;

ፀሐይን ተጎናጽፋ፦  ፀሐይ ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ  ነው። አነ ብርሐኑ ለአለም /እኔ የአለም ብርሐን ነኝ እንዳለ/
ጨረቃን ተጫምታ፦ ጨረቃ ቅዱሳን : ጻድቃን ሰማእታት ናቸው። በሳይንሱ ጨረቃ የራሱ የሆነ ብርሐን አለው እንዴ? የለውም ነገር ግን ከፀሐይ ብርሐን reflect ወይም አንፀባርቆ በማታ ያበራልናል። ቅዱሳኑም ብርሐንን ፀሐይ ከሆነው ከጌታ ለጨለማዋ አለም ያበራሉ። ብርሐነ አለም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደምንል። እኔ የአለም ብርሐን ነኝ ያለው ጌታ ፃድቃንንም አንትሙ ብርሐኑ ለአለም
/ እናንተ የአለም ብርሐን ናቹህ/ ብሏቸዋልና። በአንድ ጨለማ ክፍል ያለን ሻም ብናጠፋው ጨለማው የሚብሰው ባጠፈነው በራሳችን ላይ ነው፤ መናፍቃንም እንደሻማ እየቀለጡ የሚያበሩትን ጻድቃንን ቢቃወሙ ጨለማው የሚብሰው በራሳቸው ላይ ነው ማለት ነው።  
ጨረቃን ተጫምታ፦ አንድም ጨረቃ የእመቤታችን የክብሯ መገለጫ ነው። አንድም እመቤታችን የፃድቃን የሰማእታት ሞገሳቸው ክብራቸው ናትና ጨረቃን ተጫምታለች።

 12 ከዋክብት ያለበት አክሊል የተቀናጀች፦ የእመቤታችንን ቅዱስ ሥዕል ስንመለከት በራስዋ ላይ 12 ከዋክብት ያለበት አክሊል አለ; አሥራ ሁለቱ ከዋክብት ብርሐነ አለም የሆኑት የአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ምሳሌዎች ናቸው። እመቤታችን የሐዋርያቱ ሞገሳቸው ናትና፤

አንቲ ውእቱ እህቶሙ ለመላእክት ትንቢቶሙ ለነብያት ሞገሰ ክብሮሙ ለሐዋርያት እሞሙ ለሰማእታት እንዲል

እመቤታችን የመላእክት እህት የነብያት ትንቢት የሐዋርያት ሞገስ የጻድቃን እናታቸው ናትና!!!

ለመጀመሪያ ጊዜ የእመቤታችንን ቅዱስ
ሥዕል የሳለው ወንጌላዊው ሉቃስ ነው።
የእመቤታችን ጸጋ አይለየን
አሜን

                                                     

/ተክለ መድህን/











No comments: