Friday 9 August 2013

// ጾም //



ዝንቱ ዘመድ ኢይወጽዕ ዘእንበለ ጾም ወበ ጸሎት // አብሮ አደግ አጋንንት ያለጾምና ጸሎት አይወጣም፤ ማቴ 17፦21

// ጾም //

ጾምሰ እማ ለፀሎት
ወእህታ ለአርምሞ
ወነቃየ ለአንብዕ

ጾም የፀሎት እናት፣ የተመስጦ እህት ፣ ለንስኃ እንባ ምንጭ ናት!

መዝሙረ ዳዊት 6
1 አቤቱ፥ በቍጣህ አትቅሠፈኝ፥ በመዓትህም አትገሥጸኝ።
2 ((ድውይ ነኝና አቤቱ፥ ማረኝ)) አጥንቶቼ ታውከዋልና ፈውሰኝ።
3 ነፍሴም እጅግ ታወከች አንተም አቤቱ፥ እስከ መቼ ድረስ ነው?
4 አቤቱ፥ ተመለስ ነፍሴንም አድናት፥ ስለ ቸርነትህም አድነኝ።
5 በሞት የሚያስብህ የለምና፥ በሲኦልም የሚያመሰግንህ ማን ነው?
6 በጭንቀቴ ደክሜያለሁ ((ሌሊቱን ሁሉ አልጋዬን አጥባለሁ፥ በዕንባዬም መኝታዬን አርሳለሁ))
7 ((ዓይኔ ከቍጡ ዕንባ የተነሣ ታወከች ከጠላቶቼ ሁሉ የተነሣ አረጀሁ))

ዳዊት ሆይ የንስኃ እንባህ ክቡር ናት!!

የደጋጎቹ አለቃ ክቡር ጴጥሮስ ሆይ እንደ ጅረት ወንዝ ያነባኸው እንባ ክቡር ናት!

ሳናውቅ ከሰራነው በድፍረት የበደልንህ እጅጉን በልጧልና አቤቱ ሆይ ይቅር በለን።

መሥዋዕተ አበው ዕጣነ ዘካርያስ የተቀበልክ አምላክ
የኛንም ተቀበል ምስጋናና ፀሎት፤ አሜን።

http://yonas-zekarias.blogspot.com/

No comments: