Tuesday 6 August 2013

//ከልጅነት እስከ ሽምግልና//



አባታችን አዳም ከህቱም ድንግል መሬት ከተፈጠረባት ሰከንድ ጀምሮ አምላኩ እግዚአብሔር ነበር። አባታችን ያዕቆብ ከልጅነቴ ጀምሮ የመገበኝ እግዚአብሔር ብሎ እምነቱን መሰከረ። ዳዊት ተቀበለውና ከማህጸን ጀምሮ አምላኬ ነህ ብሎ ይበልጥ አጸናው! 

ዳዊት በበገናው ከማህጸን ጀምሮ አምላኬ ነህ እንዳለ ከማህጸን ጀምሮ እስከ ሽምግልና አምላካችን እግዚአብሔር ነው። 

ትንቢተ ኢሳይያስ 46
3 እናንተ የያዕቆብ ቤት ሆይ፥ የእስራኤልም ቤት ቅሬታ ሁሉ፥ ከሆድ ያነሣኋችሁ ከማኅፀንም የተሸከምኋችሁ፥ ስሙኝ።
4 እስከ ሽምግልና ድረስ እኔ ነኝ፥ እስከ ሽበትም ድረስ እሸከማችኋለሁ እኔ ሠርቻለሁ እኔም አነሣለሁ እኔ እሸከማለሁ እኔም አድናለሁ።

/1/ ዘመዶቻችን ሆይ ኢየሱስ ክርስቶስ አምላኬ ነው ብላችሁ የምታምኑት ከስንት ዓመታችሁ ጀምሮ ነው?

2ኛ ወደ ጢሞቴዎስ
3፥15 ((ከሕፃንነትህም ጀምረህ ክርስቶስ ኢየሱስን በማመን፥ )) መዳን የሚገኝበትን ጥበብ ሊሰጡህ የሚችሉትን ቅዱሳን መጻሕፍትን አውቀሃል።

/2/ ጢሞቴዎስ ከልጅነት ጀምሮ ኢየሱስ ክርስቶስን ያምናል። እናንተስ ከልጅነት ጀምሮ ክርስቶስን ታምናላችሁን?

ወደ ዕብራውያን
8፥11 እያንዳንዱም ጐረቤቱን እያንዳንዱም ወንድሙን። ጌታን እወቅ ብሎ አያስተምርም (( ከታናሹ ጀምሮ እስከ ታላቁ ድረስ ሁሉ ያውቁኛልና።))

/3/ ከታናሽነታችሁ ጀምሮ ክርስቶስን ታውቃላችሁን?

/4/ የያዕቆብ መልእክት 2፦19 አጋንንት ደግሞ ያምናሉ ይንቀጠቀጡማል።
አጋንንት ያምናሉ የእናንተ ልጆች ምን ያምናሉ?

http://yonas-zekarias.blogspot.com/

No comments: