Wednesday 21 December 2011

"ገድለ ሐዋርያት"


ስለ ፃድቃን ሰማእታት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በእብራዊያን መልእክቱ በተከታታይ ምዕራፍ ላይ ይናገራል።
 /እብራዊያን ምዕራፍ 11; 12 እና 13/
 

+++ እብራዊያን 11:34 አለም ለነሱ አልተገባቸውምና በየበረሀው በየዋሻው ተንከራተቱ።

ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ ጻድቃን በየበረሃው ተንከራተው እንዳለፉ ነገረን; አሁንም በሀገራችን በየገዳሙና በበረሐው ጤዛ ልሰው ዳዋ ጥሰው ዋእይ ቁሩንም ታግሰው ለሃገር ለህዝብ የሚፀልዩ አበው አሉን። ሃገራችን ብትታረስ ብዙ ጻድቃን የሚበቅሉባት ቅድስት ሃገር ናትና። መናፍቃን ግን ገዳማዊ ህይወትን ይቃወማሉ; ታላቁ ሐዋርያ ግን በመልክቱ አለም ለፃዳቃን እንዳልሆነች ነግሮናል።
+++ እብራዊያን 12:1፦ ብዙ ምስክሮች በዙሪያችን አሉን።
ሐዋርያው ሰማእታትን ምስክሮች አላቸው; ሰማ መሰከረ ሰማእትነት ምስክርነት ማለት ነው።
በእብራዊያን 11:37 ላይ እነ ነብዩ ኢሳያስ በመጋዝ ለሁለት ተሰንጥቀው ሰማእትነት እንደተቀበሉ ገለጸና እነዚህ ሁሉ ምስክሮች /ሰማእታት/ በዙሪያችን አሉ አለን።
በነፍሳቹ ዝላቹ እንዳትወድቁ የጸናውን አስቡ; እብራዊያን 12:3; ሐዋርያው የጸኑትን ሰማእታትን እንድናስብ ይመክረናል።

እብራዊያን 13:7፦ የእግዚአብሔርን ቃል የተናገሯችሁን ዋኖቻችሁን አስቡ፤ የእምነታቸውንም ፍሬ እየተመለከታቹ በሕይወትቸው ምሰሏቸው።
 ብዙ ግዜ የወደቀውን ነው የምንመስለው ነገር ግን የጸኑትን እነ ነብዩ ኢሳያስን እነ አባ ተክለ ሐያማኖትን; ሰማእቱን ቅዱስ ጊዮርጊስን መምሰል እንዳለብን ይመክረናል።

        “ገድለ ሐዋርያት”






ሐዋርያው ቅ/ጴጥሮስ




   ቁልቁል በመስቀል ላይ ተሰቀለ




ሐምሌ 5 ቀን 67 ዓ.

ሐዋርያው ቅ/ጳውሎስ
በሮም ከተማ በኦስትያ መንገድ አንገቱን ተሠይፎ ዐረፈ

ሐምሌ 5

ሐዋርያው ዩሐንስ
በንጉስ ድምጥያኖስ በፍጥሞ ደሴት በፈላ ውሃ በበርሜል ውስጥ ተሰቃየ

ሞትን አልቀመሰም

ሐዋርያው በርተለሜዎስ
ከነህይወቱ አፈር በተሞላ ከረጢት ውስጥ ከተው ወደ  ባህር ወረወሩት

መስከረም 1
ሐዋርያው እንድርያስ

በግሪክ ሃገር
በ X መስቀል ላይ ተሠቅሎ ሞተ

ታህሳስ 4

ሐዋርያው ቶማስ
በጆንያ ውስጥ አፈር ሞልተው ጨው ነስንሰው መንገድ ለመንገድ ውሻ እንዲበላው አደረጉት

66ዓ:
ሐዋርያው ያዕቆብ ወልደ ዘብዴዎስ
ሄሮድስ አንቲጳስ በሠይፍ አስገደለው
በ44 ዓ.ም የሐዋ. 12:2


ሐዋርያው ያዕቆብ ወልደ እልፍዮስ
ከቤተ መቅደስ ጫፍ ወርውረው በድንጋይ ደብድበዉት ዐረፈ
         
            የካቲት 10

ሐዋርያው ይሁዳ /ታዴዎስ/
መጽሐፈ ሄኖክን በመጥቀሱ የመጽሐፍ ቅዱስ ቁጥር 66 ብቻ አለመሆኑን አስረድቷል

  
     የይሁዳ መልዕክት  ቁ 8
ሐዋርያው ናትናኤል /ቀነናዊው ስምኦን

በሠይፍ አንገቱ ተቀላ
ሰማዕትነት ሲቀበል ሰማይ ተከፍቶ
የሥላሴን ክብር አይቷል ዩሐ. 1:51

ሐዋርያው ፊሊጶስ

በስቅላት ዐረፈ


ከዲያቆን ፊሊጶስ ይለያል የሐዋ 6:5

ሐዋርያው ማቴዎስ

አንገቱን ተሠይፎ ዐረፈ


ኢትዮጲያ መቶ ያስተማረ ሐዋርያ ነው

ሐዋርያው ማትያስ
በብረት አልጋ አስተኝተው ከስሩ ለ 7 ቀናት ያህል እሣት ለቀቁበት

በይሁዳ ምትክ የተተካ ሐዋርያው ነው

ወንጌላዊው ሉቃስ
በጆንያ አፈር ሞልተው ጨው ነስንሰው ወደ ኤዥያን ባህር ጣሉት

ወንጌልና የሐዋርያትን ሥራ ፅፏል

ወንጌላዊው ማርቆስ
በግብፅ ሃገር ከሠረገላ ጋር አስረው ቀን ሙሉ እየጎተቱት ልብሱ ተቀዶ ስጋውም እንደልብስ ተቆዶ ዐረፈ

ሚያዝያ 30

ነብዩ ኢሳያስ
ድንግል በድንግልና ትጸንሳለች ብሎ ሲተነብይ በመጋዝ ለሁለት ተሰንጥቆ ሰማእትነትን ተቀበለ

           እብራዊያን 11:34

መጥምቁ ዩሐንስ

በሔሮድስ አንገቱ በሰይፍ ተቀላ


ማቴ 14:10

ጲላጦስ ሰማእት
ከደሙ ንፁህ ነኝ ብሎ የጌታን ትንሳኤ በመመስከሩ አንገቱን በመሰየፍ ዐረፈ
Oxford Christian dictionary

ቅ/ፖሊካርፐስ

በእሣት ተቃጥሎ ሞተ

ራዕ 2:9

 ቅ/አንቲጳስ

በንጉስ ድምጥያኖስ በነሓስ መጥበሻ ተጠብሶ ሞተ

ራዕ 2:13

ቅ/ሌንጊኖስ

አንገቱን ተሠይፎ ዐረፈ
የጌታን ጎን በጦር ሲወጋ የጌታ ማየ ገቦ ሲነካው እውር የነበረ አይኑ በራ አናም አመነ

አላዛርና እህቶቹ
በቀዳዳ መርከብ ጭነው ወደ ባህር ጣሉት

በጌታ ትእዛዝ ከሞት ተነስቶ ነበር

ሊቀ ዲያቆናት ቅ/እስጢፋኖስ
በድንጋይ ተወግሮ ዐረገ

ድዳና መስማት የተሳነውን ባገኘ ግዜ እፍ እያለ ይፈውስ ነበር!!!

ቅ/ጊዮርጊስ

አንገቱን በሠይፍ ተመትሮ ዐረፈ

ሚያዝያ 23

ኢትዮጲያዊው ጃንደረባ /ባኮስ/

ወደ ጋዛ አካባቢ እያስተማረ እያለ በሠማዕትነት ዐረፈ
በአለም ለመጀመሪያ ግዜ ጥምቀትን የተጠመቀ ፤ የመጀመሪያው አፍሪካዊ ሐዋርያ ነው!!!

ያስቆርቱ ይሁዳ

ለዚህ ክብር አልተገባውም





 
ሐዋርያቱ ከአንበሳ ጋር ሲታገሉ ነገሥታቱ እየተዝናኑ  የሚያዩበት ስቴዲዮም የሚመስለው ቦታ ይህን ይመስላል


ከሐዋርያቱ አንድም እድሜን ጠግቦ የሞተ የለም፤
እንዲሁ በሰማዕትነት አለፉ እንጂ!

የጻድቃን በረከት ከሃገራችን "ኢትዮጲያና ኤርትራ" አይለይ፤ አሜን!
                                                         
             
/ተክለ መድህን/