Friday 16 December 2011

"መቆምና ማየት"

አንድ የተከበሩ አባት እንዲህ ብለው ጠየቁ፤

መላእክት እንደ ሰው የሚታጠፍ እና የሚዘረጋ እግረ ሥጋ የላቸውም፤ ታዲያ መላኩ ቅ/ገብርኤል እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ ሲል ምን ማለቱ ነው?? ሉቃስ [1: 19]  

በእርግጥ ግሩም ጥያቄ ነው፤ መላእክት መንፈስ ናቸውና እግረ ሥጋ የላቸውም፤ አይቀመጡም አይነሱም አይቆሙምም!  
ሊቀ መላእክት ቅ/ገብርኤል እኔ በእግዚአብሔር ፊት የምቆመው ገብርኤል ነኝ ማለቱ ምህረትን ጠያቂ አማላጅ ነኝ ሲል ነው። እንዴት ማለት ጥሩ ነውና እንዴት? እንበል

ይህን እንድንረዳ ልበ አምላክ ዳዊት የዘመረውን አብረን እንይ፤  የተመረጠው ሙሴ በእግዚአብሔር ፊት ባይቆም” ኖሮ ሕዝበ እሥራኤላዊያን በቅጽበት በጠፉ ነበር ይለናል መዝ. [105:23] ሙሴ ቀጥ ብሎ ስለ ቆመ አይደለም እስራኤላዊያን የተማሩት፤ ሕዝቡን ከምታጠፋ ሥሜን ከሕይወት መጽሐፍ ላይ ደምስስ!!! እያለ የለመነው ልመና ነው እስራኤላዊያንን ያስማራቸው ፀአት[32:32]

ስለዚህም መቆም” ማለት ቀጥ ብሎ መቆም ብቻ ሳይሆን  መለመን ፣ ማማለድ እንደሆነ ባህረ ጥበብ የሆነች ቤተክርስቲያናችን እንዲህ ከመጽሐፍ ቅዱስ እየያበሰለች ትመግበናለች!
እስኪ በአንድምት እንምጣ፤ አንድም ስለ ሕዝቡ የሚቆመው ታላቁ አለቃ ሚካኤል ይነሳል ዳንኤል [12:1] ቅ/ሚካኤል እግረ ሥጋ የለውም፤ ስለ እኛ ምህረትን ይለምናል እንጂ። አንድም መላዕክትም በእግዚአብሔር ፊት ለመቆም መጡ፤ ሰይጣንም በመካከላቸው ነበር። ኢዮብ [1:6] ሰይጣን ከሳሽ ስለሆነ ቆመ አልተባለም መላዕክቱም ቆሙ የተባሉት ቀጥ ብለው ቆሙ ለማለት አይደለም፤ ሊለምኑ መጡ ለማለት ነው እንጂ።  አንድም እግርህ በድንጋይ እንዳይመታ በእጆቻቸው ያነሱሃል ይላል፤ መዝ. [90: 11] መላዕክት እንደ ሰው እጅ የላቸውም መንፈስ ናቸውና፤ ነገር ግን ሎጥን ከሰዶም እሣት እጁን ይዘው እንደወጡ ፈጥነው ደራሽ መሆናቸውን ሲያስረዳን ነው። አንድም መላዕክት እንደ ሰው የሚያዩበት ዓይነ ሥጋ የላቸውም፤ መንፈስ ናቸውና፤ በወንጌል ግን ጌታችን እንዲህ አለ፦ ከታናናሾቻችሁ ማንንም እንዳትንቁ ተጠንቀቁ ጠባቂ መላእክቶቻቸው ዘወትር የአባቴን ፊት ያያሉና ማቴ. [18:10] ያያሉና ማለት ዓይንን ገልጦ ማየት ማለት አይደለም፤ መላዕክት ዓይነ ሥጋ የላቸውም ተብሏልና። ያያሉ ማለት ይለምናሉ ማለት እንደሆነ አየህን?

አንድም “ጠባቂ መላእክቶቻቸው” የሚለውን ስንመለከት ጠባቂ የሚለቅ ቃል መላዕክት ጠባቂ እንደሆኑ አይነግረንምን? አንድም መላእክቶቻቸው የሚለው ቃል እያንዳንዱ ሰው ፪ ዑቃቢ መልአክ /ጠባቂ መልአክ/ እንዳሉት አይነግርህምን? ፩ዱ በቀን ሲጠብቅህ ፩ዱ በለሊት እንደሚጠብቅህ አታውቅምን?

የጥቅስ ጥናት ዘዴ
የቅ/ሚካኤል በዓል የሚውለው በ 12 ነው ስለዚህ ዳንኤል [12:1]
የቅ/ገብርኤል በዓል የሚውለው በ 19 ነው ስለዚህ ሉቃስ [1: 19]

·       ቁልፍ ቃላት መቆም ፣ “በእጆችቸው ያነሱሃል”፣ “ማየት”



26 comments:

Bine Man said...

lemenafekan yetesete tiru melse

Adane Girma said...

Delicious tnks ma friend.

Bruk Dulla said...

Bene tsidk sayhon bekidusanu milja nw yalehut. Kibir lekidusan.

Talew Adola Dheressa said...

That is great thanks

Tamerat Hailu said...

kale heyewet yasemalen mengesete semayaten yawereselen

Fikresilase Adane said...

What an Interesting cotemmplated idea! May God bless u.

Temesgen Woldeyesus said...

Kalehiwot yasemalin!!! le tiakeye melse agignchalew

Elsa Yohannes Mengistu said...

really betam betam amesgenalew may God bless you yena wendem kale heyewet yasemalen. mengeste semayaten yawerselen

Yohannes Mehari said...

I really Like it ! We expect more from u, coz i can c that u can. May God Be with u! Amen !!!

Orange Chuchu Crown said...

Kalehiwet yasemalin des yemil timhirt new asbeaw alawkim neber!

Mulusew Andualem said...

hey how are u doing? i am doing fine. thank you very much for your
message. God bless you for ever. it is the time that we should stand truly
for our Sunday school and our church!!! be strong in faith and action to
take possible efforts ...to strength our Sunday schools every where,
especially in county sides!!!
please message me if there is new.
thank u!
God bless u!!

Melashu Aragie said...

In our country we are traying to sing only saint yared song in every sunday school.z new thing is zise.

Helina said...

"betam naw yatadasatekut lamen endanante heywot wset nabarekuge enanatam tsnat yesetachu amen be talotachu asebun amen..............."

Abel H Mariam said...

Thank you so much ma dear bro for your post! GOD BLESS YOU!! sele kedus paulos bezu neger mawek efelgalew ena pls post me about st.paul

Bili Mehari said...

K h y.betam betam des yemil astemari new berta wendme amlak mistrun yeglesleh.

Kokobe wrote: said...

"Ewnet talak timhrt new.kale hiwetn yasemaln,Egziabhar yagelglot zemenhn ybarkln!!!"

Tigist Tsegaye said...

wnedemachn:---ysmayun mna amelak ymgebhe,bert,ejeg btme true tmhert nwe ystlalfekwe sgawen yabezalehe

Richo Gizaw said...

tafach,yemayitegeb yeabatoch temhert endih betwaza melku siqereb emayitegeb new.qal hiwet yasmalen wendem yona

Richo Gizaw said...

leabatochchen tisgawen yadel amlak berktachewen yadelen.QHY

Bili Mehari said...

wendme edmena tena yesteh maryamen new yemleh betam new yastmarkegne kenezih hulu alwashem yegiorgisen,yepetrosen,yepawlosen bech neber yemawkew astemrehegnal berta egziabher mistrun yeglesleh tebarek wendme.
21 hours ago via mobile · LikeUnlike · 2

Arsema Kebede said...

kalat yigalal tirgum gin yadinal endalut likawuntu andimtawun awkan erasachinin ka sihitatna kalamawak yirdan amen kala hiwot yasamalin

Elizabth Teklehana said...

ታድለህ ወንድሜ!!!
ሰንበት ትምህርት ቤትህን ከል መውደድ ማለት ትልቅ ሰማዕትነት ነው፡፡ ምክንያቱም በዚህ ዘመን ወጣት ሆኖ ለሰንበት ትምህርት ቤት
ከል የሆነ ፍቅር ስለማይገኝ ነው በእውነት ፍቅርህ ከል እንዲሆን የቅዱሳን አምላክ ይርዳህ! ለእኛም ጸልይልን በማስመሰል ሳይን
ከልብ በመነጨ ፍቅር ሰንበት ትምህርትቤታችንን እንድንወድ ይርዳን አሜን፡፡
7 hours ago via · UnlikeLike · 2

Yared Abebe · Friends with Emuya Desalegn and 3 othersLoading... said...

Yared Abebe · Friends with Emuya Desalegn and 3 othersLoading...
Betam des yelal tebarek lastemaren amelak mesegana yegebaw aref temert nat

Anonymous said...

good staff good start

Anonymous said...

"betame dese yemele temerete newe geta yebareke"

Genet said...

"betame dese yemele temerete newe kelebe ahmesegenalewe geta yebareke