Friday 30 December 2011

“ታናሽዋ ደመና”




“ታናሽዋ ደመና”  
 ከአ.አ - ለንደን ኤርፖርት

 “አሁን ባላችሁበት ዘና ብላችሁ ተቀመጡና አንድ ታሪክ ልንገራችሁ”

 አውሮፕላን ውስጥ ነው ያለነው፤  ከሩቅ የምናየውን ደመና እያሳየን ጓደኛዬ ዘካርያስ ታሪክ እየነገረን ነበር፤  እኛም ትንሽ ደክሞን ስለነበር ደስ አለን … /፤/

ግዜው የፈረንጆቹ አዲስ አመት ነበር፤ እነሆ ከኢትዮጲያ አየር መንገድ ተነስተን ጉዞ ወደ ለንደን ጀመርን። እኔና ጓደኛዬ ዘካርያስ አውሮፕላኑ ውስጥ እንደገባን ትንሽ አረፍ አልንና ለረጅሙ መንገድ ያዘጋጀነውን መፅሐፍ አውጥተን ማንበብ ጀመርን፤

ለትንሽ ግዜ ካነበብን በኋላ ከአጠገባችን የተቀመጠችው አንዲት ልጅ ለመግባባት ብላ “ ሔርሜላ እባላለሁ የምታነቡት መፅሐፍ ምንድን ነው?” ብላ ጠየቀችን በጨዋ ፈገግታ፤ እኔ የማነበው ነገረ ማርያም /Mariology/ የሚል ነው አልኳት ገፁን ለማሳየት እየሞከርኩ፤ ዘካርያስም የእኔ ደግሞ “ቤተክርስቲያንህን እወቅ” ይባላል አላት።
እርስ በእርስ ለመተዋወቅ ብዙ አልፈጀብንም፤ ሶስታችንም በስደት ሃገር ስለምንኖር ስለሃገር ቤት ናፍቆት ብዙ ተነጋገርን።

ደኛዬ አሁን ባላችሁበት ዘና ብላችሁ ተቀመጡና አንድ ታሪክ ልንገራችሁ” አለን እኛም ትንሽ ደክሞን ስለነበር ደስ አለን፤ ያለንባትን መቀመጫ ወደኋላ አመቻችተን ተቀመጥንና በል ንገረን አልነው፦

ከሩቅ የሚታየውን ደመና ሳይ አንድ ታሪክ ትዝ አለኝ አለንና ትረካውን ቀጠለ /1ኛው ታሪክ/



በነገሥታት ዘመን ነበር፤ ነብዩ ኤልያስ ሰማይን በፀሎቱ ለ31/2 ዓመት ዘጋ; ዝናብም አልዘነበም ነበር፤ እነሆ አንድ ታናሽ ብላቴና ይዞ ወደ ቀርሜሎስ ተራራ ወጣና እስኪ ዝናብ እንደሚዘንብ ወደ ተራራው ጫፍ ሂድና አይተህ ና ብሎ ላከው። ያም ህፃን ከሄደበት ተመልሶ መጣና አባቴ ኤልያስ ሆይ ሰማዩ ደመና የለው መሬቱ ደረቅ ነው ምንም ዝናብ የለም” አለው። ኤልያስም ተመልሰህ ሂድና እይ አለው፤ ታናሽ ብላቴናው እንዲህ እያለ ፯ ግዜ ተመላለሰ። ይህ ታናሽ ብላቴና ካደገ በኋላ ነብዩ ዮናስ ሆነ ይላሉ አባቶቼ።

ነብዩ ዮናስ በ፯ኛው የምስራች ዜና ይዞ ወደ ኤልያስ መጣና አባቴ ኤልያስ ሆይ እነሆ ገና ከሩቅ እጄን የምታክል “ታናሽ ደመና” ትታየኛለች አለው፤ ያቺ ደመና ወደ ሰማይ ወጥታ ዝናብን አመጣች! እነሆ ይህች ታናሽዋ የኤልያስ ደመና የእመቤታችን ምሳሌ ናት! አለን ዘካርያስ።

እንዴት? አልነው እኔና ሔርሜላ

እንዲህ ብሎ ቀጠለ፦

እነሆ ያቺ ታናሽ ደመና ወደ ሰማይ ወጥታ ዝናብን እንዳመጣች ሁሉ እመቤታችንም ገና የ15 አመት ታናሽ ገሊላዊት ብላቴና ስትሆን “የተጠማ ቢኖር የሕይወትን ውሃ ይጠጣና ይርካ” ያለውን ጌታን ወልዳለችና፤ አንድም ታናሽዋ ገሊላዊት ብላቴና ሰማየ ሰማያት የማይችሉትን ጌታን በማሕፀንዋ ተሸክማለችና “ታናሽዋ ብላቴና በታናሽዋ የኤልያስ ደመና ትመሰላለች አለንና ሙሉውን ታሪክ አነበበልን [1ኛ ነገሥት 18: 43]

ይህ መዝሙርስ ትዝ አይላችሁም? አለን

ክብረ ቅዱሳን ይእቲ /2/ ሙዳዬ መና ግሩም /2/
የቅዱሳኑ ክብር ነሽና
እንሰጥሻለን ቅኔ ምስጋና
የወለድሽልን የሕይወት መና
ዝናብ ያለብሽ ታናሽ ደመና”
የእኛ መዝሙር እንዲህ ትርጉም ያለው ሲሆን መልካም ነው፤ ባህረ ጥበብ ቤተክርስቲያን ገና ብዙ ያልተነካ ሚስጢራት አሏትና! እኛ ግን ሚስጢሩ ገና ሳይገባን ትታደስ የሚል መዝሙር ልናወጣ ግጥም እንገጥማለን! አዬ ከንቱ “ፍራሽ አዳሽ  ለነገሩ ጥበብ የገባው ሰለሞን በመፅሐፈ መክብብ መግቢያው ከንቱ ከንቱ የከንቱ ከንቱ ያለው የራሱ ምክንያት ቢኖረውም በዘመናችን ከንቱ ሰዎች እንደሚነሱ ታይቶት ቢሆንስ ማን ያውቃል? አለንና በረጅሙ ተነፈሰ ዘካርያስ ኡህህህ

ወደ ታናሽዋ ደመና ልመልሳችሁ”አለ ከሃሳቡ መለስ እያለ፤

ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋሥጫም በህሊናው ወደ ቀርሜሎስ ተራራ ወጣና እንደ ነብዩ ዮናስ ያቺን ታናሽ ደመና አያት፤ እንዲህም ብሎ ዘመረ፦
ኦ ርህርተ ህሊና እንተ ኤልያስ ደመና ……

/ነብዩ ኤልያስ በቀርሜሎስ ተራራ ታናሽዋን ደመና እያየ/


ይህ ታሪክ  ታላቅ ነው! አለና እነሆ ዘካርያስ ትረካውን ቀጠለ፦

የፍጥረታት መጋቢ የሆነውን የድንግልና ወተትን አጥብታዋለችና ይህ ሚስጢር ታላቅ ነው! በሳይንሱ አንዲት ሴት ለልጇ የሚሆነውን ወተት የምታዘጋጀው በፀነሰች ግዜ ነው። ሴት ልጅ የድንግልና ወተት የላትም፤ እመቤታችን ግን የድንግልና ወተትን /ሐሊብ ወተትን/ በድንግልና አዘጋጀች! አሁንም ደግሜ እለዋለሁ ይህ ሚስጢር ታላቅ ነው!   እሣታዊያን የሚሆኑ መላዕክት የማይዳስሱትን በጀርባዋ አዝላ እናትነትን ከድንግልና አስተባብራ ይዛለችና! ይህ ሚሥጢር በእርግጥ ግሩም እፁብ ድንቅ ነው!

ሌላ ትረካ ትፈልጋላችሁ? አለን ዘካርያስ እንዳንደክምበት እያሰበ
እኛም ይሁን ይጨመርልን አልነው፤ የዘካርያስ 2ኛው አዲስ ታሪክም ቀጠለ፦

ሔርሜላ በእጇ ላይ የያዘችው መፅሐፍ “አንቺ ሴት” የሚል ነበር፤ መናፍቃኑ የፃፉት ነው።  ለእሷም እንድታነበው ሰው ነው የሰጣት፤
 እንደ መግቢያ የተፃፈው ንባብ “ጌታችን ማርያምን አንቺ ሴት ብሎ ስም አወጣላት” ይላል ዘካርያስ “አንቺ ሴት” ብሎ ርዕሱድ በድጋሚ በማስተዋል አነበበልንና ይገርማችኋል ለመጀመሪያ ግዜ “አንቺ ሴት“ ያለው የመጀመሪያው ሰው አዳም ነው፤ እነሆ አዳም ከህቱም ድንግል መሬት ወይም ከአፈር ተፈጠረ፤ እግዚአብሔር አምላክም በአዳም ላይ ከባድ እንቅልፍ ጣለበትና ከግራ ጎኑ አንዲት ዐጥንት ተነቅላ ሔዋን ተፈጠረች።  አዳምም ዞር ብሎ ሔዋንን አያትና ይህች ሥጋ ከሥጋዬ ይህች ዐጥንት ከዐጥንቴ ናት ሲል “ሴት” አላት [ዘፍ. 2: 23] ጌታችንም እመቤታችንን አንቺ ሴት ሲላት ከሥጋሽ ሥጋ ከነፍስሽ ነፍስ ነስቼ የተወለድኩብሽ “አንቺ ሴት” ሲላት ነው!
አንድም አዳም ከህቱም ድንግል መሬት መፈጠሩ እመቤታችን በህቱም ድንግልና ጌታን የመውለዷ ምሳሌ ነው! አንድም ከአዳም የግራ ጎን ዐጥንት ሲነቀል አዳምን አላመመውም ነበር ይህም እመቤታችን ጌታን በወለደች ግዜ ህመም እንዳላገኛት ሲያስረዳን ነው!  
ይህ ትርጉም ግሩም ነው! ባህረ ጥበብ ቤተክርስቲያን እንዲህ ታስተምራለችና! ቤተክርስቲያንህን እወቅ የሚለውን መፅሐፍ የማነበው ለዚሁ ነው አለንና ዘካርያስ ታሪኩን ወደመጨረሱ መሆኑን አሳወቀን።

አሁን ደግሞ ከደመና ወደ ፀሐይና ወደ ጨረቃ ልውሰዳችሁ” ሲለን ሔርሜላ ሳቅ እያለች ወደ ሰማይ ቀረብ ስትል Astronomers መሆን አማረህ እንዴ? አለችው፤ ዘካርያስ ሳቅ አለና የጨረቃውን ታሪክ ለነ ዩሪ ጋጋሪን ልተውላቸውና ለዛሬ የእኔን ታሪክ ልንገራችሁ” ብሎ ይህችን ታሪኩን ነገረን፦
 ፀሐይን ተጎናጽፋ ጨረቃንም ተጫምታ በራስዋ ላይ 12 ከዋክብት ያለበት አክሊል የተቀናጀች አንዲት ሴት ነበረች” [ራዕይ 12:1] የእመቤታችን ክብር እንዲህ ይነበባል። እስኪ እያንዳንዱን ቃል በቃል እንየው አለን ዘካርያስ; እኛም ለመስማት ተዘጋጀን። እርሱም ቀጠለ፦

ፀሐይን ተጎናጽፋ፦  ፀሐይ ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ነው። አነ ብርሐኑ ለአለም /እኔ የአለም ብርሐን ነኝ እንዳለ/
ጨረቃን ተጫምታ፦ ጨረቃ ቅዱሳን ፣ ጻድቃን ሰማእታት ናቸው። በሳይንሱ ጨረቃ የራሱ የሆነ ብርሐን አለው እንዴ? የለውም ነገር ግን ከፀሐይ ብርሐን reflect ወይም አንፀባርቆ በማታ ያበራልናል። ቅዱሳኑም ብርሐንን ፀሐይ ከሆነው ከጌታ ለጨለማዋ አለም ያበራሉ። ብርሐነ አለም ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ እንደምንል። እኔ የአለም ብርሐን ነኝ ያለው ጌታ ፃድቃንንም አንትሙ ብርሐኑ ለአለም
/ እናንተ የአለም ብርሐን ናቹህ/ ብሏቸዋልና። በአንድ ጨለማ ክፍል ያለን ሻም ብናጠፋው ጨለማው የሚብሰው ባጠፈነው በራሳችን ላይ ነው፤ መናፍቃንም እንደሻማ እየቀለጡ የሚያበሩትን ጻድቃንን ቢቃወሙ ጨለማው የሚብሰው በራሳቸው ላይ ነው ማለት ነው። 
ጨረቃን ተጫምታ፦ አንድም ጨረቃ የእመቤታችን የክብሯ መገለጫ ነው። አንድም እመቤታችን የፃድቃን የሰማእታት ሞገሳቸው ክብራቸው ናትና ጨረቃን ተጫምታ እያለ የራዕዩ ፀሐፊ ያወድሳታል።

 12 ከዋክብት ያለበት አክሊል የተቀናጀች፦ የእመቤታችንን ቅዱስ ሥዕል ስንመለከት በራስዋ ላይ 12 ከዋክብት ያለበት አክሊል አለ; አሥራ ሁለቱ ከዋክብት ብርሐነ አለም የሆኑት የአሥራ ሁለቱ ሐዋርያት ምሳሌዎች ናቸው። እመቤታችን የሐዋርያቱ ሞገሳቸው ናትና፤
ባለበገናው ዳዊትም በገናውን እየደረደረ እግትዋ ፅዮን /ፅዮን ክበብዋት/ ብሎ ዘመረ [መዝ. 47: 12] ፅዮን ማለት አምባ መጠጊያ ማለት ነው፤ እመቤታችን ስሟን ጠርተን ምርኩዛችን ሆናለችና! ሐወርያቱም የበገናውን መዝሙር ወደዱት መሰል እመቤታችንን በመካከላቸው አድርገው ዙሪያዋን ከበው ለፀሎት ይተጉ ነበር! ያን ግዜ መንፈስ ቅዱስ ለሐዋርያቱ ወረደ! ይለናል [የሐዋ. 1: 14]


ነብዩ ኢሳያስ ስለ ፅዮን /ስለእመቤታችን/ ዝም አልልም እያለ በቤተልሔም ኤፍራታ ተገኘና
የመላዕክቱን የእረኞቹን ዝማሬ ሰማና
ናሁ ድንግል ትፀንስ እነሆ ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች አለና
የጌታን ልደት በዓይኑ ሊያይ ናፈቀና ትንቢቱ ከመፈፀሙ ከ700 ዓመታት በፊት አስቀድሞ ተነበየ፤ የዘመኑ ሰዎች አልታደሉምና እንዴት ድንግል በድንግልና ትፀንሳለች አሉና መጋዝ አመጡና ኢሳያስን ያዙና እነሆ ሥጋውን ለሁለት በመጋዝ ቆራረጡት!

“ነገር  ይፀናል በሶስት” እንዲሉ ሶስተኛውን ታሪክ ልንገራችሁና ልፈፅም አለን። እኛም ተስማማንበት፤ ፫ኛውና የመጨረሻውንም ታሪክ ቀጠለ፦
ከነብዩ ኢሳያስ ተነስተን ኤርምያስን አልፈን ሕዝቅኤልን እናገኛለን
ነብዩ ሕዝቅኤልም እንዲህ አለ፦ “በምሥራቅ የተዘጋ ደጃፍ አየሁ፤ ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች እንጂ አትከፈትም ሰውም አይገባባትም፤ የእሥራኤል ቅዱስ ሳይከፍት ገብቶ ሳይከፍት ወጥቶባታልና”[ሕዝ. 44:1]

መናፍቃኑ ይህማ ስለ ቤተመቅደስ የተነገረ ነው ይሉናል፤ ተዘግቶ የሚኖር ቤተመቅደስ አለ እንዴ? ሰውም የማይገባበት ቤተመቅደስ የለም። ይህማ ስለእመቤታችን የተተነበየ ነው፤ ትንቢቱን ልብ ብለን ስናነበው  ምን ይላል? “ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች እንጂ አትከፈትም” //በህቱም ድንግልና ጌታን ወልዳለችና//
ቅድመ ፀኒስ ወሊድ፣ ግዜ ፀኒስ ወሊድ፣ ድህረ ፀኒስ ወሊድ ድንግል ናትና፤ ወትረ ግዜ ድንግል ናትና ሲለን ነው።

አባ ሕርያቆስም በቅዳሴው ጎሳ ልብየ ቃለ ሰናየአለና
ከልቡ ምንጭ ውዳሴውን አፈለቀና “የማይናገር በግ የክርስቶስ እናቱ ገነት ደስ ይላታል”አለና ቅዳሴውን ቀደሰና አመሰገነ በግሩም ምሥጋና! የማይናገር በግ የተባለው ጌታችን ነው፤ በሸላቾቹ ፊት ዝም እንደሚል በግ አፉን አልከፈተም እንደተባለ [ኢሳ.53:7] በግ የተባለው ጌታችን ነው፤ የማይናገር በግ የክርስቶስ እናቱ ገነት” የተባለችው ደግሞ እመቤታችን ናት፤ ይህን በተመለከተ ጠቢበኛውም በጥበቡ እንዲህ አለ፦
እኅቴ ሙሽራዬ የታጠረች “ገነት የታተመች የውሃ ጉድጓድ ናት
[መሓ 4:12] “ገነት” የተባለችው እመቤታችን ናት ብለናል፤ እነሆ እነዚህ ሁሉ እናትነትን ከድንግልና ጋር አስተባብራ ስለያዘችው ስለ “ታናሽዋ የኤልያስ ደመና” የሚናገሩ ናቸውና ግሩም ናቸው! አለን ዘካርያስ አስተናጋጅዋ እንድትታዘዘን በዓይኑ እያሳየን፤ የአውሮፕላኑ አስተናጋጅ ሴትም ምን ልታዘዝ ብላ ጠየቀችን የራሳችንን ምርጫ ነገርናት፤ ምግቡ መጥቶ ከተመገብን በኋላ ለአንድ ሰአት ያህል አረፍ አልን።

This is London Heathrow airport አለን ፓይለቱ፤
 እኛም ሻንጣችንን ይዘን ወረድን። -//-

በሚቀጥለው ሳምንት “የዓለም እረኛ በግ ሆኖ ተወለደ” በሚል ርዕስ የጌታችንን ልደት በትርጓሜ እንመለከታለን
ወሥበሐት ለእግዚአብሔር





















































21 comments:

Bili Mehari said...

Endmn aleh wendme?yemtlkachew betklala betam astemari nachew sihufu rezeme lalkew yegziabher kal eko ayselechem lene betam betam temchtognal egziabher edmehen yarzmlen mastewlun yabzaleh berta selam eder

7:46pm Dec 30

Tsega Tesfaye said...

Kale hiwetn yasemaln! ketayunm begugut new yemtebkew egziabher amlak yagelglot zemenachihun yarzmew esu ybarkachihu Amen!!! 8:10pm Dec 30

Kalkidan Worku said...

Egziabher yestelen betam yasedestal ye Emebetachen amalgentuwa fikeruw berektuwa ayeleyen!!!!!!!!!

Sami Mety said...

berta

Betelihem Wubishet said...

Betelihem Wubishet ‎"khy"

Mita Belay said...

ቃለ ህይወት ያሰማልን እጅግ በጣም ግሩም ነው በርታ!

Mesfin Mamo said...

wow betame yamerale

Saba Gebre said...

Qalehiwot yasmalen!

Tadesse Yimer Neway said...

Bewint..ejig betam yemimesit kale E/R new ye EMAMLAK kibr tenegro ayalkm....kale hiwot yasemalin ...mengiste semayat yasgebalin..tebarku.

Saba Asefa said...

Enane Ashagre likes this.
4 hours ago ·

Saba Asefa like this

Abye Aylew said...

kala hiwat yasemalen

Bili Mehari said...

Endmn aleh wendme?yemtlkachew betklala betam astemari nachew sihufu rezeme lalkew yegziabher kal eko ayselechem lene betam betam temchtognal egziabher edmehen yarzmlen mastewlun yabzaleh berta selam eder

Tsegabirhan Andualem said...

ቃለ-ህይወት ያሰማልን::

Yonatan Araya said...

KHY EHUNE+

Tewo Asmare said...

egezeabhare yestilign betam amesegenalehu le wodefitem endezih ayenet tsehufochin lakilegn

Senaite Tesfaye Betham said...

des yemil tmhrt new .....kale hiwot yasemah.....ye dengl mariyam bereketua behulachn lay yder Amen!!

Bizuhan Marye said...

WONDEM Yonas Zekaris Egzeabhar Abat Ergem Edemana Tenan Yadelh Kal Hiwot Yasamlen

Moges Kahssay said...

I thank you bro. It's a great and deep lesson. God bless you.

Nahom Isak said...

GOd bless u bro KHY

Bili Mehari said...

AMEN!!!EGZIABHER kemensemawna kemnayew yealem mekera yesewren! feriha egziabher belebachen yeder!kale hiwet yasemalen tsegawn yabzaleh wendme!!!

Anonymous said...

I like your blog's name cause I can't describe how much I like my Sunday school,God bless you and your service too.May God guard Our Tewahido Faith and Church.