Saturday 8 September 2012

"ኑሮ ካሉት ፍሪጅም ይሞቃል!"

ዘና ብላችሁ ተቀመጡና አንድ ታሪክ ላጫውታችሁ! 



ከራሴ አጠር ያለች ስብሰባ አደረኩና አንድ ታሪክ ትዝ አለኝ። እናቴ ወንድሜን በቀኝ እኔን በግራ አስቀምጣየእናት ሆድ ዥንጉርጉር እንደ ነብር ጸጉርትል ነበር ወላድ ሆዷን እየዳበሰች! እኔ ደግሞጨረቃ ካለች እሩጥ እናት ካለች አጊጥብዬ ተረቱን በተረት እመልስላታለሁ። እናት ሀገሬ ኢትዮጵያ ግንየእናት ሆድ ዥንጉርጉር የሚለው ተረት አልደረሰባትም።ያልታደለ በረዶ ከድንጋይ ላይ ያርፋልእንዲል ሀገሬ አልታደለችምና ደጋፊና ተቃዋሚ ነጭና ጥቁር ረጅምና አጭር በሀገሬ ኢትዮጵያ ስማቸው እንጂ ግብራቸው የጠፋ ይመስላል። እኛ ያለን አንድ የቴሌቭዥን ጣቢያ ብትሆንም እሷምበግድ እንባ አዋጡየሚል ዜና በዛባት። አንዱ ሲደግፍ ሌላው ሲቃወም ማየት ናፈቀኝ። ደጋፊና ተቃዋሚ ማየት ናፈቀኝ።የእናት ሆድ ዥንጉርጉር እንደ ነብር ጸጉርየሚለውን ተረት ለመተረት በሀገር ቤት ብዙ እናቶች የናፈቁ ይመስለኛል።

ነሐሴ 15 ቀን 2004 . ከዚህ ዓለም በሞት መለየታቸው የተሰማው የኢ... ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ሥርዐተ ቀብር እሑድ ነሐሴ 27 ቀን 2004 . በመንበረ ጸባዖት ቅድስት ሥላሴ ካቴድራል እንደሚፈጸም ተገለጸ። እኔም የጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊን ሞት አሰብኩና ባለሁበት ሀገር የእንግሊዙ ጠቅላይ ሚኒስትር ዴቪድ ካሜሮን ወይንም የአሜሪካው ኦባማ (የሰይጣን ጆሮ ይደፈንና) ከሁለት አንዱ ቢሞቱ ኖሮ ሐዘኑ እንዴት ይሆን ነበር? ብዬ አሰብኩ። በሀገሪቱ መገናኛ ዜናው ይሰራጫል ከዚያም በክብር ይቀበራሉ አራት ነጥብ። ከአራት ነጥብ ቢዘል ሐዘኑ አንድ ቀን በቀጥታ ይተላለፋል እንጂ እንግሊዛዊያን በሙሉ ወጥተው ዕንባ አዋጡ ተብለው አይገደዱም ነበር!!

እነሱ ምንቦጣቸው እቴ። ኦባማማ የፍልፍሉን ኮሜዲ መስማት ጀምረዋል አሉ። የታደሉ እየሳቁ ይሰራሉ። የኔ ሙከራ በፍጹም የፖለቲካ ዘፈን ለመጋበዝ አይደለም። የሙዚቃ ስልቱንም አልችልበት። ለፖለቲካ እስክስታ ሲመቱ ከዐይን ያውጣችሁ የተባሉ አሉና ስራ ለሰሪው ብያለሁ። እትብቴ የተቀበረባት ሀገሬ ኢትዮጵያ ግን ሠርጓ ሠርጌ ሞቷ ሞቴ ነው። መቼስ ለእናት ሀገርያገባሽስ ይፈታሻል ይብላኝ ለወለደሽአይባልም! 


ያየ ልናገር ቢል የሰማ ላውራ አለአሉ እቴጌ ጣይቱ! ይህች ኢቲቪ የምታሳየን ደጋፊውን ብቻ ስለሆነ ጫወታው ፍዝዝ ብሏል።ያልታደለች ወፍ ዐይኗ በጥቅምት ይጠፋልእንዲሉ እኛም አልታደልን ዐይናችንና ኢቲቪ ከተጣሉ ቆይተዋል። ሞቅ ደመቅ ካለው ከእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ወደ እንግሊዝን ፓርላማ እንመለስ። የእንግሊዙን ፓርላማ ስናይ እርስ በእርሳቸው እንደ ጉድ ይከራከራሉ፣ እንደ ጉድ ደጋፊና ተቃዋሚ ይፋለማሉ፣ ጠቅላይ ሚኒስትሩን እንደ ጉድ ቁጭ ብድግ እያደረጉ በጥያቄ ያፋጥጣሉ፤ አልፎ አልፎ ሳቅ ፈገግ የሚያስብል ቃላትን ወርወር ያደርጋሉ! የእንግሊዝን ፕሪሚየር ሊግ እና የእንግሊዝን ፓርላማ ያየ ይዝናናል የሚባለውም ለዚሁ ነው። እኛ ቤት ግን ይህ ፍጹም ነውር ነው። ደጋፊ በሀገር ውስጥ ተቃዋሚ በአሜሪካ ሆነው በሁለቱም በኩል ምርጥ ምርጥ የተጋነኑ ዜናዎችን ስንሰማ ዐይናችንም ጆሯችንም ሰልችተዋል። 

ጅብ እንኳን ጓደኛውን ይጠራልአሉ እቴጌ ጣይቱ። ጅብ በለስ ሲቀናው ድምጹን ከፍ አድርጎ ሌሎችን ጅብ ይጠራል። ይህን የመሰለ እንስሳ ሆዳም ማለታችን እጅጉን ይገርማል። እባካችሁ ተለያይቶ መናከስን ሳይሆን እንደ ጅብ ተጠራርቶ መብላትን ለሀገር መስራትን አስተምሩን። እንግሊዛዊያን ስለ ውድ ሀገራቸው ስለ ታላቅዋ ብሪታንያ አንድ አባባል አላቸው።አንድ ላይ መስጠም ሳይሆን አንድ ላይ መዋኘት አለብንይላሉ። እባካችሁ ለእናት ሀገር ስትሉ አንድ ላይ ዋኙ። እባካችሁ ለእናት ሀገር ስትሉ የሐሳብ ፍልሚያ አሳዩን። የልብ ሳይደርስ እድሜ ይደርስ አሉ እቴጌ ጣይቱ።

የማንችስተርና የአርሴናል ልዩነት ጫወታውን ሞቅ ደመቅ ያደርገዋል። ሁሉም የማንችስተር ደጋፊ ቢሆን የኳስ ውበቱ በጠፋ ነበር። ሁሉም የአርሴናል ተቃዋሚ ቢሆን ኳስ ውበትዋን አጥታ መልከ ጥፉ በሆነች ነበር። የኛ ቤት ጫወታ ግን ፈዘዘ። ኢቲቪ የምታሳየን ደጋፊውን ብቻ ስለሆነ ጫወታው ፍዝዝ ቅዝዝ ብሏል። አፈር ስሆን አሁን ማን ይሙት የእንግሊዝ ቻናሎች ቢሆኑ ሁሉዕንባ አዋጡየሚል ፕሮግራም የሚተላለፍ ይመስላችኋል? መልሱን ለኢቲቪ ትቻለሁ። 

ሳያርፉ ዐረፉ

ጠቅላይ ሚንስትሩ ወደ ላይኛው ሀገር ሄደዋልና የሞተን መውቀስ ለሕሊናም አይመችም። ነፍስ ይማር ማለት ሰዋዊነት ሰብአዊነት ኢትዮጵያዊነት ነው። አንድም ሃይማኖታዊ ግዴታ ነው። ነፍስ ይማርና በአንድ ወቅት ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ 19 ዓመቴ ጀምሮ እረፍት የሚባል ነገር አላየሁምና በሀገሬ ሆኜ የትርፍ ስራ እየሰራሁ ማረፍ እፈልጋለሁ ብለው ነበር። ይህ ቢሳካ ኖሮ ሀገሬ ኢትዮጵያ በዲሞክራሲ ጎዳና ዳዴ ማለትዋ በታወቀ ነበር። ምኞታቸው አልተሳካምና ስልጣን በፈቃዱ የለቀቀ ጀግና ሀገሬ እንዳማራት ጎምጅታ እንዳማራት ትቀራለች። ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከጊዜ እጥረት የተነሳ ማንበብ እየፈለኩ ያላነበብኩት መጻፍ እየፈለኩ ያልጻፍኩት ነገሮች አሉ፤ ወደ ፊት ምን እንደሚሆን አይታወቅምና ከስር ከስሩ ማየት እፈልጋለሁ ብለው ነበር። ይሁን እንጂ አቶ ሞት ቀጠሮ ይዞ ኖሯል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ሳያስቡት ድንገት የቤተመንግስቱን በር አንኳኩቶ መጣ። የናፈቁትን ረፍት ሳያዩ ዐረፉ።ሳያርፉ ዐረፉ

እቴጌ ጣይቱን መለስ ዜናዊሳያርፉ ዐረፉስላቸው ነፍስ ይማር አሉ። ዜና እንዴት ነበር? አልኳቸው ኢቲቪ እንደማይዋጥላቸው ስለማውቅ። አዬ እንደ ስራቸው አሉ እንደለመዱት። እቴጌ ጣይቱ እገሌ እንዲህ ሆነ ሲባሉእንደ ስራውማለት ይቀናቸዋል። ምንም ይሁን ምንም ወሬ በሰሙ ቁጥርእንደ ስራውይሉ ነበር። ትልቅ አባባል ነው። የሆነው ይሁንና ኢቲቪ የምንከፍተው ግን ምን እንደሚተላለፍ እርግጠኛ ሆነን ነው! “ዕንባ አዋጡ!” የሚል ዜና ለማየት እንደሆነ እኛ ሳንሆን ቴሌቭዥኑም አሳምሮ ያውቃል!!

ዕንባ አዋጡ!”

~ // ~ ~ // ~ ~ // ~ ~ // ~ ~ // ~ ~ // ~


የልጅ ዮናስ ብሎግ አባል ይሁኑ!!  
 
38 ·   · Share · Tag Friends
·                                
·                                  
o                                                       
Weldemesekel Endashaw Felfelu Abezahew
o                                                       
Msh mahul
o                                                       
Yared Seid Felefa megebiyashen felgi
o                                                       
o                                                       
Bezi Mac ለምን ይህን በኢቲቢ አታቀርበዉም?
o                                                       
Meaza Mulatu Man biaysitelalifilet Yonas yichin cahawatahin begugut sitebabek neber enameseginalen!
o                                                       
Sami Tadesse hahahahhahah it is funny
o                                                       
Abey Abebe · Friends with Daniel Kibret and 32 others
realy funny
o                                                       
Yibeltal Mulat EWUNETI NEWWWWWWWW!!!!!!!!
o                                                       
Lamrot Moges · Friends with Daniel Kibret and 17 others
ha....ha,,, ETVen mamen zegtow new,,,,
August 31 at 5:47pm ·  · 2
o                                                       
Realy!
o                                                       
Liey Ketma wedm yoni ante endemtnorbet ager aynet netsa yehon medeya bafrikalay mechim alasbm bayhon ftrtariw ekon bederesen byi asbalehu (emegalehu) alemetadel ybal yele yeafrika eta fanta bedhnet makaset new.
o                                                       
Bini Man · Friends with Daniel Kibret and 48 others
Ewnet new be meles mot benazinm lekso selechen 10Q DANI
August 31 at 7:47pm ·  · 1
o                                                       
Where ever u go, where ever u are, who ever are the people surrownding u, dont 4get ur ethiopian, n not only remembering who u are but be it. . .and being ethiopian is much more than just useing z name of z brave women Etege Taytu n give. . . comments. . . .i rely enjoy the religeous writtings but then u ppl 4get how u started it all n u start to say wat ever u feel like just when we thought we met a great person " u". I feel z same way about ETV but i wdnt say it that way, not to mention ppl are terribley sad, wat u said is disrespective not 2 Meles or the gov't but 2 those ppl who r rely sad. Go 4 teaching us, Yonas not to impress us, that way u cud do both! Chiristna betam Kebad new. . .ahun Yonas ende befitu endefelegew ayawra miknyatum bzu sew yadamtewal. WEDAJE KIFU LINAGER FELGE ADELEM, Emamlak kante gar tihun!
September 1 at 1:51pm ·  · 1
o                                                       
Hamza Seid Yoni etegie betam temechitewugnal sle ARSENAL andneger belegn!

No comments: