Friday 3 February 2012

ነነዌ እና ዮናስ፦

ትንቢተ ዮናስ ምዕራፍ ፩
  
ለነብዩ ዮናስ የእግዚአብ ቃል መጣ
ነነዌን ለመስበክ ተነሳና ውጣ
በህዝቡ ኃጢአት ቁጣዬ እንዳይመጣ

ነብዩ ይህን ግዜ በልቡ አሰበ
የጌታ ባህሪው ይቅርታ እንደሆነ
ዮናስ ወደ ተርሴስ መኮብለል ወደደ
ወደ ከተማይቱ ምታልፍ መርከብ አየ
ዋጋም ከፈለና በመርከብ ተጓዘ።

ማን ይኮበልላል ከእግዚአብሄር መዳፍ
ወደ ጥልቁ ቢሄድ እንደንስር ቢመጥቅ
ጌታ ሁሉን ገዝቷል በኀይልና ክብሩ
ታላቅ ንፋስ መጣ ማዕበልን ይዞ
መርከቡን ቢያናውጥ ሁሉም እጅግ ፈሩ
እንዲቀልላቸው እቃቸውን ወደ ባህር ጣሉ
ወደ አምላካቸው አበርትተው ጮሁ
በጉዞው ከባድ እንቅልፍ ይዞት
ኮብላዮ ነብይ ይህን ሁሉ አላየም
የመርከቡ አለቃ ወደ ዮናስ ቀርቦ
ምነው ተኝተሃል ስንጠፋ ዝም አትበል
ሁሉ እንደለመነ ፈጣሪህን ለምን
ደግሞም ይህ ነገር በማን እንዳገኘን
በመካከላችን እጣ እንጣጣል
እጣውም ተጣለ በዮናስ ደረሰ
ማበሉ ፀጥ እንዲል ወደ ባህር ተጣለ።
በፈተና ግዜ መውጫው ይሰጠናል
ዮናስ በባህር ውስጥ አሳ ታዞለታል
በአሳ ሆድ ውስጥ ሆኖ ወደ አምላኩ ጮኸ
በአምላኩም ተሰማ ባህር ተሻገረ
ወደ አምላካቹ ተመለሱ እያለ
ታላቋን ከተማ ነነዌን ሰበከ
ንጉስ ለአምላኩ ክብሩን አዋረደ
ትንሹም ትልቁም ወደ አምላኩ ጮኸ
ቀን በነነዌ ታላቅ ፆም ታወጀ
ጌታም ለዛች ሀገር ምህረትን ሰጠ።

ነብዮ ከፀሐይ ሊጠለል ወደደ
በ፩ ቀን ተክል እጅግ ተደሰተ
በንጋታው ቢያጣታ እጅግም አዘነ
ጌታም መለሰለት እንዴት እንደሆነ
አንተ ላልዘራኸው ምታዝን ከሆነ
እኔም ለህዝቤ አዘንኩ አይተህ ተማር አለ።

የዓሣ ሆድ ውስጥ ፀሎት”
ዮናስ በዓሣው ሆድ ውስጥ ሆኖ
ወደ አምላኩ እግዚአብሔር ፀለየ፤ እንዲህም አለ፤
ተጨንቄ ሳለሁ ወደ እግዚአብሔር ተጣራሁ፤
እርሱም መለሰልኝ፤

ከመቃብሩም ጥልቅ እርዳታን ፈልጌ ጠራውህ፤
አንተም ጩኸቴን ሰማህ፤
ጥልቅ ወደ ሆነው ወደ ባህሩ መካከል ጣልኸኝ
ፈሳሾችም ዙሪያዬን ከበቡኝ፤
እኔም ወደ ቅዱስ መቅደስህ እመለከታለሁ አልኩ
አቤቱ ጸሎቴ ወደ መቅደስህ ትግባ

እግዚአብሔር ዓሣ አንበሪውን አዘዘው
እርሱም ዮናስን በየብሱ ላይ ተፋው!!!
    ትንቢተ ዮናስ ምዕ. [፪ -ፍ]

ለአጽዋማትና ለበአላት መሰረታቸው ነነዌ ነው፤
ጾመ ነነዌ ፣ ዐብይ ጾም ፣ ጾመ ሐዋርያት ሁል ግዜ በሰኞ ቀን ይጀምራሉ።
ደብረ ዘይት ፣ ሆሣዕና ፣ በዓለ ትንሣኤ ፣ በዓለ ሃምሳ ደግሞ ሁል ግዜ በእሁድ ይውላሉ።
ርክበ ካህናትና ጾመ ድህነት ሁል ግዜ ረቡዕ ቀን ይውላል። ስቅለት ሁል ግዜ በአርብ ቀን ፣ ዕርገት ደግሞ ሁል ግዜ በሐሙስ ቀን ይውላል። ጾመ ነነዌ የበረከት ጾም ይሁንልን ፤ አሜን።
     ወሥበሐት ለእግዚአብሔር [ተክለ መድህን]

5 comments:

Nahom Yiheyis said...

በጣም ማራኪና ኣስተማሪ ነዉ ።በ አግዚኣብሄር ስም ቀጥልበት።

Hiwot Tadele said...

Amen amen amen kala hiwoten yasamalen!!!!

Tsegabirhan Andualem said...

አሜን ቃለ-ህይወት ያሰማልን::

Elias Tesfaye EliI said...

I am proud to be your friend!
I think you have good base for the Biblical life. You tagged many useful articles. But I have some issues to be discussed with others who are willing and have the ability to answer my questions. I know that empty knowledge is nothing but I know also knowledge is life. Hosea 4:6.
Here is one of my questions:-
Who is Only- potent, Elshaday, Almighty, Creator, Alfa and Omega..... The Father or The Son or The Holy Spirit or The Trinity.... Who is the one that I should give worship. It is obvious that I should only worship one person. 1Timoty 2:5, Deuteronomy 6:4
I am asking not to make some conflict with you but just believing that you are capable to answer my questions as the result you support me to come out from deep confusion.
I want thank you before you act as a spiritual servant of God.
Elias Tesfaye

ዮናስ ዘካርያስ said...

Dear Elias Tesfaye Eli I am also very proud to be your friend!


For Christian it’s vital to deepened on the holy bible instead of personal opinion. From minor to major religious questions we simply need to ask the bible. What is the bible actually saying? If we know this answer we will not be shaking by any storm!

Let’s see the creation; sun has 3 parts:

Radiation light

Energy and

It’s perfectly circle


B/C sun has 3 parts we don’t say there are 3 suns in the universe! We just say there is only one sun;

* Just like this there is only one GOD who have to be worshiped. The 3 parts of the sun is an example of the Holy Father ፣ the holy son & the holy sprite.
/Liturgy of St Aba Heryaqos/


In addition these biblical chapters will help in some ways፦

Holy Father

I live in the country were Devil worshiped by many people! & some other pagans said there is no creator. When I asked them who create the tree they said it was just existed! But it’s just funny; if we look the creations there are days & nights sun rise & sun set ….. There must be something that controls this universe! This is God!




Holy son

Isaiah 9:6
Revelation 15:3



Holy sprite

Blessed all the sic by the hands of holy apostles. Acts of the Apostles 5:15 ፣ 19:12



If you need any more explanations or any other questions please bring it on & we will try to learn from it.


Have a good rest of the week